2011፡ የሙስና አገዛዝ፤ ፍርሃትና ሰም ማጥፋት
ባልፈው ኣመት: አሁንም በስላጣን ላይ ያለው ገዢ ኣስተዳደር ኢትዮጵያን በሽብርተኞች ማነቆ ውስጥ ተወጥራ እንዳለች ሃገር አድርጎ ለማቅረብ ባወጣው የልመናና የገንዘብ መቧገቻ እቅዱ ባለሶስት ክፍል የፕሮፓጋንዳ የቅጥፈት ታሪክ ‹‹አኬልዳማ›› በማለት (ወይም የደም መሬት በማለት ከአክትስ 1፡19 በመዋስ፤ የአስቆሮቱ ይሁዳ ክርስቶስን ክዶ በመሸጥ ባገኘው ገንዘብ የተገዛ መሬት) ከልብ ወለድ የማይሪቅ ትርኢት ለሕዝብ ኣቅርቦ ነበር፡፡ ይህም ትርኢት በአትዮጵያና በኢትዮጵያ ዲያስፖራ ሰዎች በሚታገዝና በሃገርም ውስጥ ባሉት የሚደገፍ የሽብር ተግባር አምባ አድርጎ ለማሳመን የተሰራ ነው፡፡ አኬልዳማ ሲጀምር በኢትዮጵያ ውስጥ ሊከሰት የሚችል በማለት የደም ጎርፍ መምጣት እንደሚችልና፤ ሸብር ዓለምን በማጥፋት ላይ ነው፡፡ ‹‹አኬልዳማ›› ሲተረት: “ሽብርተኝነት የቆምንበትን መሬት እያነቃነቀ፤ ዕለታዊ እንቅስቃሴያችንንም እየገታ መሆኑን በቅጥፈታዊ ፈጠራ ለማሳየት የቀረበ ትርኢት፡፡ አሁን እየተናገርኩ ያለሁት ስለዓለም አቀፉ ሥብርተኝነት አይደለም፡፡ እኔ እያልኩ ያለሁት በገዢው መንግስት ለኢትዮጵያ የተቀመጠውን የቅጥፈት ፕሮፓጋንዳና በዚያም ውስጥ ስለተካተተው አኬልዳማ ተብሎ ስለተቀፈቀፈው፤ ሸብርተኝነት ለኢትዮጵያ አስጊና አሳሳቢ ችግር ነው…… ስለተባለው ነው፡፡”