በእውቀቱ ስዩም ስለ ዞን 9 ጦማሪዎች፤ “የመከራችሁ
ተካፋይ ባለመሆኔ ሐፍረቱን አልችለውም”
የዞን ዘጠኝ ጀግኖች ብረሳችሁ ታሪክ ይርሳኝ፡፡ባንድ በኩል የዘመናችሁ ተካፋይ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል፡፡በሌላ
በኩል፣ የመከራችሁ ተካፋይ ባለመሆኔ ሐፍረቱን አልችለውም፡፡ያም ሆኖ‹‹በሉ እናንተም ሂዱ እኛም ወደዛው
ነው፡፡ወትሮም መንገደኛ ፊትና ኋላ ነው›› የሚለው የዓለሙ አጋ የበገና እንጉርጉሮ ባጸደነፍስ ላሉት ብቻ ሳይሆን
ባጸደወህኒ ላሉትም ይሆናል፡፡
ስሜቴን እንዴት መግለጽ እንዳለብኝ አላቅም፡፡የገላውድዮስ ዜና መዋእል ጸሐፊ
በዚህ ሰዓት የሚሰማኝ ስሜት ከምእተ አመታት በፊት ተሰምቶት ነበር፡፡
መዓልትኒ ኮነ ሌሊተ፣ዘኢነአምሮ ወጽልመት ዘኢልማድ መጽአ
ወደፈነ እንስሳ ወሰብአ
(ቀኑ ሌሊት ሆነና፣ ወጋገኑ ተሰደደ
እንግዳ ጨለማ መጣ፣ጠባዩ ያልተለመደ
ሰውን፣ እንስሳን ጋረደ)
No comments:
Post a Comment