Friday, December 27, 2013

ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊ እንሁን

      ተመልካች ሳይሆን ተሳታፊ እንሁን

ይች ሃገር ያለመሪ ነው የምትመራው ብል ማጋነን አይሆንብኝም ምክንያቱም ህዝቦች ባላችው መቻቻል እና አብሮ የመኖር ፍቅር ሁሉን አቻችለው እንዲኖሩ አድርጝቸዋል ከሁሉ የሚገርመው መንግስት አንዱን ብሄር ከሌላው ሊያጋጭ የተቻለውን ሁሉ ሲያደርግ በየብሄሩ
ያሉ ምራቃቸውን ዋጥ ያደረጉ የሃገር ሽማግሌዎች ገና ከጥንስሱ ነገሩን ያመክኑታል ልጆቻቸውን እየገሩ ሃገር ማለት ምን ማለት  እንደሆነ እየመከሩ እያስተማሩ ያችን ሃገር  ሀገር ሆና እንድትቀጥል ላደርጉ ለነዛ የሃገር ባለውለታዎች ክብር እና ምስጋና ይሁን እንደ ወያኔዎች ሃሳብማ ገና ወንበር ከመያዛቸው ሃገሪቱ እንደ ሃገር አትቀጥልም ብለው ነበር ለዚህ ነው ሁሌ ሲያስፈራሩን ልትበጣጠስ አንድ ሳምንት የቀራትን ሃገር ከመከፋፈል አዳናት እያሉ ሊዘባነኑብን የሚፈልጉት።
       በመሰረቱ ያቺ ሃገር እንደ ሃገር ልትቀጥል የቻለችው ህዝቦች ባላቸው የዘመናት የመቻቻል ባህል ነው እንጂማ ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት የተሰሩብን ደባዎች እንኩዋን ለኛ አለምን ያስገረመ ነው በዓለም ታሪክ የራሱን ህዝብ በተቀናጀ ሁኔታ ያሸበረ የመጀመሪያው መንግስት ወያኔ ።  

ከላይ ያነሳሁት ሃሣባቸው አልሳካ ሲል ሰሞኑን ደግሞ ሌላ መርዶ ሊያሰሙን ደፋ ቀና እያሉ ነው 1200 ኪ ሜትር እርዝመት ያለውን ለም መሬት ለሱዳን ለመስጠት እና የራሳቸውን የአየር ድንበር ለማበጀት መሪ ብለው ባስቀመጡት አሻንጉሊት አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ
ህዝብ ሣያውቅ እንደ ወንበዴ ውስጥ ለውስጥ ስምምነት ላይ ለመድረስ ከጫፍ ደርሰዋል 

Thursday, December 26, 2013

ያ ትውልድ እና እኛ

                      ያ ትውልድ እና እኛ

 እኔ ማለት የዘመን ክስተት ነኝ የሚገርመኝ ልጅነቴን ሳላውቀው እንደሸኘሁት
 ሁሉ ወጣትነቴም ለጎልማሣነት አሣልፍ ሊሰጠኝ ከጫፍ ያደረሰኝ ሰው ነኝ

 ሁሌም የሚገርመኝ እና የሚደንቀኝ ነገር ስለምን ያ ትውልድ አልፉታን አለ
 በራሱ የሚተማመን የራሱን አብዬት ሊያስነሳ የሚችል የሀገር ፍቅር ስሜት
 ከውስጡ የሚፍለቀለቅ ትውልድ ስለምን መሆን አቃተን እንዴትስ በሁሉም አቅጣጫ
 ያ ትውልድ ስለምን ተቆጣጠረን የሚለው የዘወትር ጥያቄዬ ነው

Sunday, December 8, 2013

ልማት ወይስ ስጋት ?

         
             ልማት ወይስ ስጋት ?


ወያኔ-ኢሕአዴግ ያገሪቱን የኢኮኖሚ አውታር በሰፊው በመቆጣጠር፣ በዙሪያው ለተሰባሰቡ የጥቅም አጋሮቹ
የማየርነጥፍ የሃብትና የንዋይ ጎተራ ሆኖላቸዋል፡፡ ሰፊው ሕዝብ የእለት ጉርስ አሮበት፣ መታከሚያ ቸግሮት፣ ፍትህና ርትእ ርቆት በችግር በሚጉላላበት ሰአት፣ ወያኔና አሽከሮቹ በድሎት እየተንደላቀቁ ሕዝብ ላይ ማግሳት ከጀመሩ ከ21 አመታት በላይ ሆኗል፡፡ በዚህም አገሪቱ በጥት ጠመንጃ ነካሽ ያገር ጠላቶች እጅ ወድቃ በመማቀቅ ላይ ትገኛለች፡፡

አገራችን በእንዲሀ አይነቶቹ የቀን ጅቦች መዳፍ ስር ወድቃ ወዴትም ልትራመድ የማትችል በመሆንዋ ቀጣ እጣ ፈንታዋ ሁሌም አሳሳቢ ሁኖ ይቀጥላል፡፡  የሀገሪቱን ቀጣይ ሂደት ወቅታዊውን የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና የማህበራዊ እድገት የሚያቀጭጭ ብቻ ሳይሆን፤ በሀገሪቱ ታሪካዊና ብሄራዊ ኩራቶች ላይ ሁሉ ትልቅ ስጋት የሚደቅን ነው፡፡ ይህ በጠመንጃ ላይ የተመሰረተ የግፍ አገዛዝ፣ ከአለማቀፉዊ የመረጃ ፍሰትና የንቃተ ህሊና
እድገት ጋር በፍፀም ሊጣጣም የማይችል ነው፡፡ የሰውን ልጅ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በዘመናዊ ባርነት ቀንበር ስር ለመግዛት የሚያደርገው ጥረት ባጭሩ መቀጨት ያለበት ነው፡፡

Thursday, December 5, 2013

ስሟ በውቅያኖስ ተሰይሞላት እንዳልነበር


ስሟ በውቅያኖስ ተሰይሞላት እንዳልነበር

ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ታሪክ ባለቤት ናት ሲባል አንዳንድ ኢትዮጵያዊ እንዲሁ ሀገራችንን ስለምንወድ ብቻ የሚወራ ይመስለው ይሆናል። እውነቱ ግን ይሄ አይደለም፡፡ በእውነትም አገራችን የሚያኮራ ታሪክና ገድል ያላት ጥንታዊት አገር ነች፡፡
ባንድ ወቅት የደቡብ አትላንቲክ ውቅያኖስ ኢትዮፒክ ውቅያኖስ ይባል እንደነበር ስንቶቻችን እናውቅ እንደሆነ አይታወቅም፡፡ ይሄ እድሜ ጠገብ ውቅያኖስ በእርግጥም የደቡቡ ክፍል “ኢትዮፒክ ውቅያኖስ” ይባል እንደነበር የታሪክ ተመራማሪዎች ያሰምሩበታል፡፡ ይህ ደቡባዊ ያትላንቲክ ውቅያኖስ ክፍል እስከ አስራ ዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ባገራችን ስም ስያሜ ይጠራ እንደነበርም ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡

ይህን ለምሳሌ ያህል በመጥቀስ ያንድ ወቅት ታላቅ ሕዝብና አገር ባለቤቶች እንደነበርን ለማሳየት ሞከርኩ እንጂ፤ የኢትዮጵያን ታላቅነት በዝርዝር ማሳየት ካስፈለገ ብዙ ሌሎች ምሳሌዎችን መጨመር ይቻላል፡፡ ኢየሩሳሌም ያሉትን ገዳማት ጨምሮ ባገራችን ያሉ ብዙ ጥንታዊ ገዳማት፣ አብያተ ክርስቲያናት ታሪካዊ ስፍራዎች እንቁ ጌጦቻችንና መታወቂያችን ናቸው፡፡  በወርቃማው የፈርኦን ዘመን እኩል ሥልጣኔ የነበረን ታላቅ ሕዝቦች እንደ ነበርን፤ ያክሱም ሐውልት ቋሚ ሕያው ምስክር ነው፡፡ የላሊበላ ውቅር አብያት ክርስቲያናት፣ የጎንደር ቤተ መንግስቶች፣ የሶፍ ኡመር ዋሻና የመሳሰሉት ድንቅ የታሪክና የተፈጥሮ ቅርሶቻችን መኩሪያዎቻችን ናቸው፡፡

ኢትዮጵያ አገራችን የአፍሪካ የነፃነት ምልክትና አርማ እንዳልነበረች ሁሉ፤ ዛሬ በኛ ትውልድ ዘመን፤ ፔትሮ ዶላር ያሰከራቸው አረቦች መቀለጃና መጫወቻ ሆናለች፡፡ ለዚህ ደሞ ማረጋገጫው በቅርቡ በሳውዲ አረቢያ መንግስትና ወሮበሎች አማካኝነት በዜጎቻችን ላይ የደርሰው ውርደትና ስቃይ ነው፡፡ ዜጎቻችን ተገለዋል፣ ታስረዋል፣ ተቀጥቅጠዋል፣ ተዘርፈዋል፣ ተደፍረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከዚህ የበለጠ በደልና ውርደት በታሪኳ ውስጥ አይታይም ሰምታም አታውቅም፡፡

የወያኔ ሹማምንት ከድሃ ሕዝባችን ላይ እየዘረፉ በውጭ ባንኮች ውስጥ ያከማቹትን ገንዘብ የትየለሌ ሆኗል፡፡ ለዚህ ምሳሌው የነአዜብ ጎላና የመሳሰሉት የውጭ ባንክ ገንዘብ ክምችት ነው፡፡ ድሮ በነቢልጌት የገንዘብ መጠን እንደመም እንዳልነበረ ሁሉ፤ ዛሬ ደሞ በራሳችን ብር ጌቶች በነአዜብ ቱጃርነት መደመም ጀምረናል፡፡

በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ፤ ዛሬ መሬታችን ለውጭ ባለሀብቶች እየተቸበቸበ፣ ሕዝባችንን ጦም አዳሪ ያደረገ የወያኔ አስከፊ ስርአት አለ፡፡  ባለመሬቱ ያገር ሰው እይተፈናቅል እነካራቹሪና አረብ ቱጃሮች እርስቱን የመበዝበዣ መሳሪያ አድርገውታል፡፡ የሳውዲ እስታር የተባለው ኩባንያ አገራችን ውስጥ ትልቅ የርሻ ቦታ ይዞ የኛን ዜጎች ደሞ የገላል፣ ያስራል፣ ይዘርፋል፣ ይደፍራል….

የወገኖቻችንን ጉዳት የተመለከተው የአዲስ አበባ ህዝብ የሳውዲን መንግስት ለመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በወጣበት ጊዜ፤ መንግስት ተብዬው ሰልፉን አግዶ ካረቦቹ ጎን ተሰለፈ፡፡ ይሄኔ ነው ባገር ቤትም በውጪም ያለነው ሁሉ፣ ለዚህ ውግናችን ማን ይድረስለት ማን ያስጥለው ከጅቦቹ እያልን ጩኸት የጀመርነው፡፡  

 ኢትዮጵያ የታሪክ ባለሀብት ብቻ አይደለችም፡፡ አሁንም ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ብናየው
እንዃን የብዙ ሙህራን ባለቤት ናት ። የሀገራችን የሰብአዊ መብት ጥሰት ሁኔታ አስገድዶቸው
አብዛኞቹ ከአገራቸው ተሰደው ባእድ አገርን እያገለገሉ የሚኖሩ ይገኛሉ።  የአገራቸው
ጥፋትና ጉዳት ውስጣቸውን እየበላ በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለሚመለከተው ክፍል ያስታዉቃሉ፣ የጮሃሉ፣ ይታገላሉ… ከዚህም በተጨማሪ በሀገር ፍቅር ናፍቆት ውስጣቸው እየተቃጠለ የሚሰቃ ብዙዎች ናቸው።

እኛ ኢትዮጵያውያን ከዚህ በላይ ውርደትን ለመቀበል ህሊናችንን ልንፈቅድለት አይገባም፡፡ በኳስ ላይያሳየነውን አንድነት ግማሹን እንኳን አምባገነኖችን ለማስወገድ ፋይዳ ብንጠቀምበት፤ የደስታችንን ምንጭ በራሳችንን እጅ እንደጨበጥን ይቆጠረ ነበር፡፡ ስለዚህ ህብረታችንን
ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ማጠንከር ይኖርብናል፡፡የዚህችን ታሪካዊ ሀገር ክብር የማስመለስ

ብሔራዊ ግዴታ እሁላችንም ዘንድ አለና መጠንከር አለብን ።

                                                 ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር


ከምናሴ መስፍን
ከኖሪቤ ኦስሎ

Thursday, November 21, 2013

የህወሓት እኩይ ተግባር እያደረ ይገለጣል!!

 (ኢንጂኔር አብደልውሀብ ቡሽራ - መቀሌ)
ከሁለት ሳምንታት በፊት ወደ ሽሬ ለመሄድ ወደ መቀሌ አውቶብስ ተራ ሄድኩና በሰላም ባስ አውቶብስ ተሳፍሬ ጉዞየን ጀመርኩ:: እየተጓዝን እያለን በተቀመጥኩበት ወንበር አጠገብ ሁለት ሰዎች ነበሩ:: ሰዎቹ ከዛ በፊት አይቻቸው አላውቅም:: ሁለቱም አካል ጉዳተኞች ናቸው:: በመንገዳችን እየተጓዝን እያለን ሁለቱ ሰዎች የድሮ ትዝታቸው እያነሱ እያወሩ ነበሩና እኔም የነሱ ወሬ አዳምጥ ነበርኩ:: እንደዛ ቆየሁና ወሬያቸው ታሪካዊና የድሮ ትዝታቸው ስለጣመኝ በመሃላቸው ገባሁና ተዋወቅኩዋቸው:: እነዛ ሰዎች ሁለቱም የቀድሞ
የህወሓት ታጋዮች የነበሩና በትግሉ ጊዜ አካላቸው የተጎዱ መሆናቸው አወቅኩ:: እንደዚህ እያወራንና
እየተጨዋወትን ረጂም ጊዜ አለፈ:: በጨወታችን ማሀል አንዳንድ ጥያቄዎች አቀርብላቸው ነበር:: እነሱም
ለምጠይቀውን መልስ ይሰጡኝ ነበር:: በመቀሌ ከተማ ፍረስወአት የሚባል የእንጨትና የብረት ሥራዎች
የሚሰራና ሥራው በአካለ ጉዳተኞች የሚካሄድ ድርጅት አለ:: ከአስር ዓመት አካባቢ በፊት በድርጅቱ ብዙ ረብሻዎች የሥራ ማቆም አድማና ሰላበማዊ ሰልፍ ለማድረግ ሙከራ እንደአደረጉና በፀጥታ ኃይሎች እንደታገዱ አውቅ ነበር:: በዛን ጊዜ ያን ችግር በሚመለከት ብዙ ጊዜ በጋዜጦች ፅፌ ነበር:: የችግሩ መነሻ የሆነው በድርጅቱ ብልሹ አስተዳደርና በሰራተኞች መካከል የነበረ የአሰራር ብልሹነት ችግር ምክኒያት ነው:: ምክኒያቱም የአስተዳደር ሥራ በአካለ ጉዳተኞች ያልሆኑ ሰዎች ይካሄድ ስለነበረና እነሱ ደግሞ የሚፈጥሩት ችግር ነው:: ይህን ሁሉ እያነሳን ብዙ አወራን ሃሳብ ለሃሳብ ተለዋወጥን::

Tuesday, November 12, 2013

”ኢትዮጵያዊ መልኩን ነብር ዥንጉርጉርነቱን ሊቀይር ከቶ ይቻለዋልን?”





ኢትዮጵያዊ መልኩን ነብር

ዥንጉርጉርነቱን ሊቀይር
ከቶ ይቻለዋልን?”
(ትንቢተ ኤርምያስ 13:23)

                                                                                                                                     
 -ከምናሴ መስፍን - ኖርዌይ
በዚች ባለንበት ፕላኔት ላይ የሰው ልጅን አስተሳሰብ ወይም ህገ ልቦና ከሚዳኙት ረቂቅ ክንውኖች መሀከል የስነ መለኮት ወይም የስነ ፅሁፍ ሀብቶች ውስጥ ታላቁ መጽሐፍ (መጽሐፍ ቅዱስ) አቢዩ ነው። ታላቁ  ይናገራል።
ምንም እንኩዋን በአገራችን የኢትዮጵያን ታሪካዊ ጠላቶች ዘመቻ - ከውጭም ሆነ ከውስጥ እኩይ ጡት ነካሽ ልጆችዋም የሚሰነዘሩ፤ ዘርፈ ብዙ እርሷነትዋን የማጥፋት ዘመቻዎች እጅግ ይበዛሉ፡፡ ያም ሆኖ እነርሱ እራሳቸው እንቅልፍ ያጣሉ እንጅ አምላክ በቃል ኪዳኑ ስለሚጠብቃት አንዳች አትሆንም።

Thursday, May 30, 2013

Meles Zenawi and our money



The last seven years or so I have been writing opinion pieces on the political situation in our homeland. Naturally I have discussed the late Prime Minter Meles Zenawi and his central role in charting the direction our country should follow on the road he envisioned to improve the life of our people. Prime Minter Zenawi ruled over our country for twenty one years. One can say from 1991 when the TPLF took over to 2001 when the split within the party took place in the aftermath of the Eritrean Conflict the TPLF operated in a primitive semi democratic group type of leadership which they brought over from their days fighting the Derg.
The split that took place in 2001 changed the dynamic of the ethnic based outfit. It did not take long for Meles Zenawi to assert his position as the Capo di tutti capi (boss of all bosses) in the Mafia outfit that was masquerading as a political party until his death in 2013. The 2005 General election was another defining moment in the relationship between the TPLF Party and Meles Zenawi on one hand and the people of Ethiopia on the other.
Meles Zenawi in the company of other billionaires From 1992 to 2004 Meles Zenawi and his party were busy redrawing the map, rewriting our history, granting independence and redefining our national priorities and felt comfortable in their accomplishments. In fact they were so sure that they have constructed a solid foundation that will withstand any and all challenge by what they thought to be a desperate amalgamation of discredited and demoralized opposition that they allowed an open semi free election. Meles called the move “a calculated risk.”  Obviously it exploded and back fired on his face.

ዓባይና የመለስ ዜናዊ (ወያኔ) ታላቁ ሴራ



ሰሞኑን የአለምንና የኢትጵያውያንን ሀሳብና አስተየት ለመለዎጥ ወይም ለማሳሳት ወያኔ በወኪሎቹ አማካይነት የተለመደዉን ፕሮፓጋንዳ ሲነዛ ከርሞአል። ዓባይ እንደሚጠቅመን ሆኖ ቢገደብልን እጂግ ደስ ይለን ነበር። የወያኔ ትግሬዎች ሰለአባይ ከባለቤቱ ከኢትጵይያ ህዝብ በላይ የሚያቀነቅኑበት የሚጮሁበትና ሚያስመስሉበት ምክንያቱ ሌላ ነው። እነሱ ሃገር ወዳድ ሌሎች ኢትዮጵዉያን ሀገራቸዉ ብታድግና ብትጠቀም የሚጠሉ ሆነው አይደለም።
የኢትዮጵያም ህዝብ ይህንን በደንብ ያዉቀዋል። ከእባብ እንቁላል እርግብ ኣልጠብቅም ብሎአቸዋ። ታዲያ ይኸ ሁሉ የአዞ እንባ ማፍሰስና የኢትዮጵያን ሀዝብ ጩኸት ለመቀማት የመሞከር ሚስጥሩ ምንድነው??? ወያኔ ኢትዮጵያን ለመጉዳትና ለረጂም ጊዜ እችግር ዉስጥ ለማስገባት ካስጠናቸዉ ትልልቅ ጉዳዮች (ፕሮጀችቶች) ኣንደኛዉና ዋናው የአባይ ግድብ ነው። ለዚህም ማስረጃ የሚከተሉትን ነጥቦች ተመልከቱ:
ሀ) ግድቡ የሚሰራው በጥንቃቄ የመሀል ሀግሩን ህዝብ በተለይም አማራዉንና ኦሮሞዉን እንዳይጠቅም በጣም እርቆ በጠረፍ ላይ ነዉ። ይህም በተለይ አማራዉና ሌሎች በአካባቢው የሚኖሩ ህዝቦች በምንም አይነት ለእርሻ (ለመስኖ) ለመጠጥ ለኢንዱስትሪና ለኤሌክትሪክ ኣገልግሎት እንዳይጠቀሙ ታስቦ የተሰራ ነው።

Tuesday, May 28, 2013

“አባይ ይገደብ፤ ኢህአዴግም ይገደብ፤ አባይ ይቀየስ ኢህአዴግም ይቀየስ!”




“የዘመናት ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሰራዊት ከዚህ በፊት ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን የሬድዮ ጣቢያ ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ተቆጣጥሮታል፡፡ ጉንቦት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ መህረት!” አለ ታጋዩ…
“የዘመናት ብሶት የወለደው ጀግናው የኢህአዴግ ሰራዊት ከዚህ በፊት ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን የሬድዮ ጣቢያ አሁን ደግሞ ለራሱ ጥቅም ተቆጣጥሮታል፡፡ ቆጣጥሮታልም፤ ግንቦት ሃያ ሺ ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሶስት አመተ መህረት!” አልኩ እኔ…
“ኢህአዴግ ደርግን ደመሰሰ እና ሌላ ቀዳበት” አለ ልጅ ያሬድ! ”ኢህአዴግ ደርግን ደምስሶ በደርግ ዜማ ሌላ ቀዳበት” አልኩ እኔ
ዛሬ ግንቦት ሃያ ነው፡፡Abe Tokichaw (Abebe Tolla) the Popular Ethiopian Political Satirist
አነዛ ፀጉራቸውን አሳድገው አዲሳባ የገቡ ሰዎች ዲሞክራሲን እና መልካም አስተዳደር ያሳድጉልናል… ብሎ ተስፋ የጣለባቸው ሁሉ በቴስታ ብለው ከጣሉት እነሆ ሃያ ሁለት አመት እንደዋዛ ሆናቸው፡፡
መልካም አስተዳደሯንም ለራሳቸው እያደሯት፤ ዴሞክራሲዋንም ራሳቸው እየኮመኮሟት ህብረተሰቡን እንቁልጭልጭ አሉት፡፡
ዛሬ የግንቦት ሃያ በዓል ሲከበር የአባይ ወንዝን የማስቀየስ ስራ ይሰራል ተብሏል፡፡ ወንዙ ተቀይሶ ምን ላይ ሊሆን ነው… እንዴት ነው ነገሩ በሳፋ ነው እንዴ ግድቡ የሚሰራው… ብዬ ልጠይቅ ወይስ አልጠይቅ…!
አስታውሳለሁ፤ “አባይ ይገደብ በቃ” ብለው ጠቅላዩ የወሰኑት ከሁለት አመት በፊት “በቃ” በሚል ሀይለ ቃል …ኢህአዴግ ይበቃዋል ግንቦት ሃያን ዘንድሮ ለመጨረሻ ጊዜ እናከብራለን ከዛም ለድጋፍ ሰልፍ ወጥተን በዛው እንቀራለን፡፡ ኢህአዴግ እስካልወረደ ድረስም እቤታችን አንገባም…. የሚል እንቅስቃሴ በፌስ ቡክ በኩል ተጀምሮ የነበረ ጊዜ ነው፡፡
በዚህ በ”በቃ” ጦስ እነ ርዮት አለሙ እነ ውብሸት ታዬ እነ አቶ ዘሪሁን ገብረ እግዚአብሄር እነ ሂሩት ክፍሌ ወድያው ለእስር ሲዳረጉ ቀስ በቀስ ደግሞ ሌሎችም ለቃሊቲ እና ለቂሊጦ ተዳርገዋል፡፡ (በተለይ የነዚህ ወዳጆቼን ፍርድ ሂደት ስከታተል ነበር እና አጋነንክ ቢሉኝም ባይሉኝም የአቃቤ ህግ ማስረጃ “በቃ የሚለውን የፌስ ቡክ እና የአደባባይ እንቅስቃሴ ትኩር ብላችሁ አይታችኋል” የሚል ነበር)
እንቅስቃሴው በፌስ ቡክ ተጀምሮ በየአደባባዩም “በቃ” የሚል ሃይለቃል በመፃፍ ተሟሙቆ የቀጠለ ነበር፡፡ በርካቶችም ግንቦት ሃያ መስቀል አደባባይ የሚፈጠረውን ተዓምር እያሰቡ አንድም ደስታ አንድም ፍርሃት ሲፈራረቅባቸው አንደነበር ትዝ ይለኛል፡፡
ይሄኔ አቶ መለስ ፈርሸው ዘየዱ፤ (ሁል ጊዜ ቁጭ ብለው አሰቡ… እያልንኮ ፍራሽ የሌላቸው አስመሰልናቸው… “ፈርቸው” ማለት ፍራሽ ዘርግተው እጅግ በተመስጦ ማሰብ ማለት ነው…) አስበው አስበውም፤ “ለምን አባይን አንገድበውም…” አሉ እርሳቸው ብለው እምቢ… እንዴት… ለምን… በምን… አይባልምና እሺ እሺ ተብሎ ተጀመረ፡፡ የዛን ጊዜውን ግንቦት ሃያም መንግስታችን ለአባይ ግድብ ድጋፍ ሰልፍ ውጡልኝ፡፡ አለ… በዛውም የህዝቡ የተቃውሞ ሃሳብ ተገደበ፡፡
የአቶ መለስን ብልጠት በመኮረጅ ፈተናዎች ይታለፋሉ ብለው የሚያምኑት አቶ በረከት ደግሞ ዛሬ እነሆ በግንቦት ሃያው አባይ ወንዝን የማስቀየስ ስራ እነደሚሰራ በቴሌቪዥናቸው ብቅ ብለው ነገሩን፡፡
ጥሩ ኮርጀዋል…! አኮራረጃቸው ስም ሁሉ ሳይቀር እንደሚቀዳ አይነት ኮራጅ ነው፡፡
ህዝቡ ይህንን ዜና ሲሰማ ምን አላቸው… የሚለውን ቤት ለቤት ሄደን መጠየቅ ብንችል ጥሩ ነበር፡፡ መጠየቅ ባንችል ግን መጠርጠር እንችላለን እና አንዲህ እንጠረጥራለን፤
“አባይ ይገደብ፤ ኢህአዴግም ይገደብ፤ አባይ ይቀየስ ኢህአዴግም ይቀየስ!” ሳይላቸው አይቀርም፡፡

ለብዙ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 20 ካለፈው ይልቅ መጪውን የሚፈሩበት ጊዜ ነው


ዛሬ ግንቦት 20 ነው።ግንቦት 20 የኢትዮጵያ የፖለቲካ መዘውር የተዘወረበት ለመሆኑ አሌ አይባልም። ዕለቱ እንደ አቶ ሃይለማርያም የመጀመርያ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ እንዳደረጉት ንግግር ” ኢትዮጵያ ልትበታተን ስትል የዳነችበት ቀን” ነው ለብዙ ኢትዮጵያውያን ግን ግንቦት 20 ካለፈው ይልቅ መጪውን የሚፈሩበት ጊዜ ነው።ይህንን ሁለተኛውን ሃሳብ እኔም እጋራዋለሁ። ካለፈው ይልቅ መጪው ይቀርበናል።ያለፈውማ አለፈ።መጪው ግን ቢዘገይም ቢፈጥንም አይቀርም።እና ግንቦት 20 ካለፈው ይልቅ ለመጪዋ ኢትዮጵያ እንዴት አስጊ ያደርገዋል። ይህንን ለማብራራት ግንቦት 20 እንደ ሀገር ለኢትዮጵያ ይዞት የመጣውን በጥቂቱም መጥቀስ ይፈልጋል።ስለተሰራው የመንገድ እርዝመት፣ህንፃ፣ወዘተ ማተት ይቻላል።እርግጥ ነው መንገድ ተስርቷል።ህንፃ ተገንብቷል።ከተሞች ሰፍተዋል።ይህ ሁሉ  ግን መጪውን አስፈሪ ጊዜ ለሀገር ከመተው አልገታውም።
መጪውን አስፈሪ የሚያደርገው የግንቦት 20 ውጤቶች ምን ምን ናቸው?
እንድሜ ለግንቦት 20 ብዬ ብጀምርስ-
  • እድሜ ለግንቦት 20 ዛሬ ኢትዮጵያ በአለም ታይቶ በማይታወቅ መልክ በቁጥር ተከልላ ክልሎች ስለ ድንበሮቻቸው ሲደራደሩ አንዳንዴም ሲጋጩ ለማየት በቅተናል። ምሳሌ የአፋር እና ትግራይ፣ የሱማሌ እና ኦሮሞ፣ የአማራ እና አፋር ወዘተ መጥቀስ ይቻላል።
  • እድሜ ለግንቦት 20 አንድሰው ከአንዱ የሃገሪቱ ክልል ተነስቶ እንበል ደቡብ ወይንም ጅጅጋ  ገብቶ መሬት ገዝቶ ልረስ ወይንም ልነግድ  ቢል እርሱ ከመምጣቱ በፊት ከ 60 እና 70 አመት በፊት የሰፈሩቱ ከጉርዳፈርዳ፣ጋምቤላ፣ጅጅጋ እና አሶሳ ካለምንም ካሳ ሲባረሩ ያያል እና መጪው እያስፈራው አይሞክረውም።
  • እድሜ ለግንቦት 20 ወላጆች ልጆቻቸውን በፈለጉት ቋንቋ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ለማድረግ በታሪካዊ አጋጣሚ የሚኖሩበት ክልል ቋንቋ ውጭ እንዳይስተምሩ ታግደዋል።ለምሳሌ ኦሮምኛ ተናጋሪ ልጁ በአማርኛ እንዲማር ቢፈልግ ግን በኦሮምያ ክልል ቢኖር አማርኛ ወደምነገርበት ክልል መሄድ ብቸኛ አማራጩ ነው።በምዕራቡ አለም የሚኖር አንድ ኢትዮጵያዊ ግን ልጁን በሀገሩ ቋንቋ እንዲያስተምር ባህሉን እንዲጠብቅ ድጋፍ ይደረግለታል።
  • እድሜ ለግንቦት 20 ኢትዮጵያ ወደብ አልባ ሆና የባህር ኃይሏን በትና  30 እና 40 ኪሎሜትር እርቀት የባህሩ ማዕበል ሲማታ እየተሰማ ከ85ሚልዮን በላይ ሕዝብ ወደብ አጥቶ የጅቡቲን እና የሱዳንን ወደቦች በከፍተኛ ገንዘብ እንዲከፍል ተወስኖበታል፣
  • እድሜ ለግንቦት 20  ጦርነት ቆመ በተባለበት ጊዜ በአዲስ አበባ ብቻ ከ 100ሺህ በላይ ”ጎዳና ቤቴ” ያሉ ሕፃናት መንገድ ላይ ፈሰው ኃላፊነት የሚወስድ መንግስት አጥተው ለማየት የበቃነው በግንቦት 20 ፍሬ ነው። (በቀድሞው መንግስት የተመሰረተው የሕፃናት አንባ እንዴት በአሁኑ መንግስት እንደፈረሰ ይህንን ሊንክ ከፍተው ቪድዮውን ይመልከቱ (http://gudayachn.blogspot.no/2013/05/main-play-list-on-home-page-playlist.html)፣
  • እድሜ ለግንቦት 20 ከሃያ ሁለት አመት በፊት ”የጫት ቤት” ብሎ በር ላይ መለጠፍ የምያሳፍርባት አዲስ አበባ ዛሬ ጫት በየዘርፉ ”የበለጩ ፣የባህርዳር፣ የወልሶ ጫት ቤት” ብቻ ተብሎ ሳይሆን የሚለጠፈው ”ጫት እናስቅማለን፣ እንፈርሻለን” ተብሎ የተፃፈባቸው ባብዛኛው ትምህርት ቤቶች የሚገኙበትን ቦታ ፈልገው የሚከፈቱ የጫት ቤቶች በዝተው ለመታየት በቅተዋል። ምን ይህ ብቻ ዩንቨርስቲዎቻችን በየዶርሙ ጫት ሸጉጠው ሲገቡ- ሲ ቃምባቸው ደጉ መንግስታችን በዝምታ አልፎ ትውልዱን ጫት ቃሚ አድርጎታል።
  • አድሜ ለ ግንቦት 20 ምሳ ሰዓት ላይ ከቢሮ ወጥተው ጫት ቅመው የሚመለሱ የባንክ ሰራተኞች፣መሀንዲሶች ወዘተ አፍርቷል ግንቦት 20።ከደንበል ህንፃ ጀርባ የሚገኙ የመቃምያ ቦታዎችን ብንመለከት በምሳ ሰዓት ደንበል ህንፃ የሚሰሩ ምሁራን ዩንቨርስቲ ሳሉ በተፈቀደላቸው የመቃም መሰረት ሥራ ከያዙ በኃላም ለመላቀቅ ትቸግረው ይታያል።እረ  እንዲያውም በሥራ ሰዓት ሾለክ ብለው የሚቅሙ ሰራተኞች መኖራቸውን የእዚህ ፅሁፍ ፀሐፊ እማኝ ነው። እድሜ ለግንቦት 20።
  • እድሜ ለግንቦት 20 ወላጅ አልባ ሕፃናት ጎዳና እንዳይወጡ በሕዝቡ የሚደገፍ እንደ ሕፃናት አምባ መስርቶ ከማሳደግ ይልቅ ለአንድ ሕፃን እስከ 25000 ዶላር መንግስት እየተቀበለ በጉዲፈቻ ስም ለአሜሪካ እና አውሮፓ የተቸበቸቡት እና ብዙዎች በህሊና ስቃይ እና የማንንነት ጥያቄ እንዲሰቃዩ የተደረጉት በግንቦት 20 ፍሬ ነው (ሰኔ 25/2012 እአአቆጣጠር  በቢቢሲ ድህረ ገፅ ላይ በወጣ አንድ ዘገባ መሰረት ኢትዮጵያ በአመት 5ሺህ በላይ ሕፃናት በማደጎነት ወደ አሜሪካ  ብቻ እንደሚሄዱ  እና አሜሪካ ከዓለም ላይ በማደጎነት ከምትወስደው ሕፃናት ኢትዮጵያውያን ሕፃናት ከ አምስቱ አንዱ እንደሆኑይገልፃል።(http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-18506474)
  • እድሜ ለግንቦት 20 ሴት እህቶቻችን ተስፋ ቆርጠው ለአረብ ሀገር ባርነት  በአስርሺዎች የተጋዙት በሄዱበት ሀገርም ስበልደሉ የሚሰማቸው አጥተው አሳር ፍዳቸውን የሚያዩት ከግንቦት 20 ፍሬ ወዲህ ነው።
  • እድሜ ለግንቦት 20 ”የኤርትራ ጥያቄን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት የሚቻለው የ ሻብያን ሃሳብ በመቀበል ነው” ብለው ስያግባቡን የነበሩት  አቶ መለስ- ጦርነቱ አበቃ ከተባለ ከ ሰባት አመታት በኋላ ለዳግም እልቂት ”ድንበር” በሚል ሰበብ ዳግም የኢኮኖሚ ፀባቸውን ወደ ወታደራዊ ግጭት ቀይረው በአስር ሺዎች የረገፉት በ ግንቦት ሃያ ውጤት ነው፣
  • እድሜ ለግንቦት 20 ስደት ቀድሞ የነበረ ቢሆንም በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ በባህር፣በእግር ወዘተ ወጣቱ ከሀገር የሚወጣው ከግንቦት 20 ፍሬ ወዲህ ነው (ወደየመን በጀልባ ተሳፍረው ከገቡት ስደተኞች ከ 70%በላይ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽን በዘንድሮው ዘገባው መጥቀሱን ልብ በሉ) ፣
  • እድሜ ለግንቦት 20 ወጣቶች ተምረው በእውቀታቸው ሀገርንም መጥቀም ሲገባቸው፣የስራ ዕድል የሚያገኙበት ወይንም  ስነልቦናቸውን የሚጠብቅ ግን ለፈጠራ የሚያዘጋጅ የስራ መስክ ከመፍጠር ይልቅ በምረቃቸው ጊዜ (የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ  2004ዓም ምረቃ ላይ አቶ ጁነዲን ለተማሪዎቹ እንደተናገሩት)ከዩንቨርስቲ ሲወጡ  የኮብል ስቶን ሥራን መስራት እንደሚገባ የተነገራቸው በግንቦት 20 ውጤት ነው።
  • እድሜ ለግንቦት 20 በሚድያውስ ቢሆን (ጎረቤት ኬንያን ለማነፃፀርያ እንጠቀም) ኬንያ የህዝብ ብዛቷ 30 ሚልዮን ሲሆን እኛ 85 ሚልዮን መሆኑን እናስታውስ እና ኬንያ በይዘታቸውም ሆነ በአቀራረባቸው የመንግስት እጅ ያልተጫናቸው 8 የቴሌቭዥን ጣቢያ፣ 38 ራድዮ ጣብያዎች፣ ከእሩብ ሚልዮን በላይ አንባቢ ያላቸው በየቀኑ የሚታተሙ 4 ጋዜጦች (http://www.pressreference.com/Gu-Ku/Kenya.html#b) ሲኖሩ ሃሳብን የመግለፅ መብት እና በሀገሪቱ የፖለቲካ ጉዳይ ላይ የመወያየት ነፃነት ከእኛ ጋር ሊወዳደር የማይችል መሆኑን ስናስብ እና ጋዜጠኞች መንግስትን ወቀሱ ተብለው በአሸባሪነት ዘብጥያ መውረዳቸውን ስናስብ እድሜ ለግንቦት 20 እንላለን።
  • እድሜ ለ ግንቦት 20 ጋና ነፃነቷን ስታገኝ የገነባነው ስታድዮም ዛሬ ጋና ከነፃነት አልፋ እስከ መቶ ሺሕዝብ የሚይዝ ስታድዮም ስትገነባ እኛ አሁንም አንድ ለእናቱ በሆነ ስታድዮም መገኘታችን የግንቦት 20 ውጤት ነው።እርግጥ ነው በዛሬው የግንቦት 20 በዓል የስፖርት አካዳሚ ምረቃ በአል እየተከበረ ነው። ስታድዮምስ ?
  • እድሜ ለግንቦት 20 ቀድሞ ጉቦ የሚለው ቃል ሲነሳ ስለ 20 እና 30 ብር ጉቦ እናስብ ነበር። ዛሬ ጉቦ፣ሙስና እና ዝርፍያ ማለት አድገው ተመንድገው  ዝርፍያ ማለት የብሔራዊ ባንክን የወርቅ ክምችት በወርቅ መሰል ነገር መቀየር ሲሆን ጉቦ ማለት ደግሞ የሀገር መሬት እና ውሃን  ለሕንድ እና ለአረብ በርካሽ መቸብቸብ ፣ በባለስልጣናት ቤት እንደባንክ ቤት በኢይሮ ብሉ በዶላር ቢሉ በፈለጉት የገንዘብ አይነት ከቤት ማስቀመጥ ማለት ነው (በቅርቡ የግምሩክ ባለስልጣናት ቤት  ተገኘ የተባለውን ብር ያስታውሱ)።
ይህንን ሁሉ ስናስብ ነው እንግዲህ ግንቦት 20 ካለፈው ይልቅ መጪውን የሚያስፈራ የሚያደርግብኝ።ከሁሉ የከፋው ግን መንግስት ስለሰራሁት መንገድ እና ድልድይ ስታመሰግኑኝ መስማት ብቻ ነው የምፈልገው ከማለቱም በላይ መሰረታዊ ስህተቶችን ”የጨለምተኞች አመለካከት’፣ የአመለካከት ችግር” እያለ ማጣጣሉን መቀጠሉ ነው አሳዛኙ።

Thursday, May 16, 2013


“ለምን ገደልከን?” የሚለው የሰማዕታት ድምፅ ይ

በባህርዳር አንድ የፌድራል ፖሊስ አባል በመንግስት ሚድያ 12 ሰዎች በሌሎች ዘገባዎች እስከ 18 ሰው ግንቦት 4/2005ዓም መፍጀቱ ይታወቃል።የግድያው ምክንያት በደንብ አልተብራራም።”ከፍቅረኛው ጋር በነበረው ጥል ነው” የተባለው ብቻ ምክንያት ነው እንዳይባል በመንገድ ላይ ሲሄድ የነበረን ሰው፣መብራት በርቶበት ያገኘው ቤት ውስጥ ያሉ ነዋሪዎችን፣በአውቶቡስ ከጎንደር አቅጣጫ የመጡ የነበሩ መንገደኞችን አስወርዶ ወዘተ ነው ድርጊቱን የፈፀመው።
Photo Fortune December 4/2011
Photo Fortune: December 4-2011

ሚያዝያ 27-የኢትዮጵያ ትንሳኤ!


ዘንድሮ (ማለትም 2005 ዓ.ም) የትንሳኤ በዓልና የሚያዝያ 27ቱ የድል በዓል ተገጣጠሙ፡፡ ባሕረ ሃሳብ እንደሚያሳየው ከሆነ የትንሳኤ በዓልና የሚያዝያ 27 ቀኑ የድል በዓል በ1994 ዓ.ም ተገጣጥመው ነበር፡፡ ወደፊትም በ2016 ዓ.ም፣ በ2089 ዓ.ም፣ በ2100 ዓ.ም፣ በ2184 ዓ.ም፣ እና በ2263 ዓመተ ምህረትም ይገጣጠማሉ፡፡ ሁለቱ በዓላት ከመገጣጠማቸውም በተጨማሪ የሚያመሳስላቸው አንድ ቁብ አለ፡፡ ያለ ፍርድና ያለ ምንም ሃጢያቱ ሰሞነ-ሕማማቱን ተሰቃይቶና ተንገላቶ በቀራኒዮ ዓደባባይ የተሰቀለው ኢየሱስ ክርስቶስና፣ ያለጢያቷ የወልወል ግጭትን ሰበብ አድርጎ ፀብ በጫረው ፋሺስታዊ ኃይል ፍዳዋን ያየችው ኢትዮጵያ፣ ማይጨው ላይ ሙሉ-ለሙሉ ከተፈታች በኋላ ፋሺስታዊ እባጭ ጫንቃዋን ነክሷት ያለ ፍርድ የተገደለችበት በመሆኑ ነው፡፡ ሞትን ድል አድራጊው ክርስቶስ በሦስተኛው ቀን፣ በዕለተ ሰንበት ከሙታን መካከል እንደተነሳ ሁሉ፣ የኢትዮጵያም ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ነፃነት ከአምስት የጽልመት ዓመታት በኋላ ዳግም ትንሳኤውን አገኘ፡፡ ያም ዕለት ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም ሆነ፡፡ የነፃነት ችቦ የተለኮሰበትና የኢትዮጵያም ትንሳኤ የተረጋገጠበት ዕለት ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም ሆነ፡፡
ከአምስት ዓመታት በፊት በሚያዝያ 27 ቀን 1928 ዓ.ም የፋሺስትን ግፈኛ ድል ለማብሰር፣ ማርሻል ባዶሊዮ አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አስወርዶ፣ ቀይ-ነጫና-አረንጓዴውን ባንዲራ የሰቀለበት ቀን ነበር፡፡ ልክ በአምስት ዓመቱ፣ ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም ደግሞ ንጉሠ ነገሥቱ በከፍተኛ አጀብ እኩለ ቀን ስድስት ሰዓት ላይ ከታላቁ የዳግማዊ ምኒልክ ቤተመንግሥት ዓደባባይ ላይ አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን ሰንደቅ ዓላማችንን መልሰው ሰቀሉት፡፡ የክብር ዘብ ተሰልፎ፣ በራስ አበበ አረጋይ የሚመራው አስር ሺህ አርበኞች ያሉት ጦር ዙሪያውን በሀገር ፍቅርና በብሔራዊ ስሜት እንደቆፈጠነ፣ በሱዳን በኩል የመጣውና በሻለቃ ዊንጌት የሚመራው የጌዲዮን ጦርም ተሰልፎ፣ መድፍ ተደጋግሞ እየተተኮሰ ሰንደቃችን በክብር ከፍ አለ (ዘውዴ ረታ፣ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት፡፡ 2005 ዓ.ም፣ ገጽ-409/10)፡፡ የኢትዮጵያ የብሔራዊ ነፃነት ትንሳኤና የመላ ሕዝቦቿም ድል አድራጊነት (ታሪክ ሠሪነት) ተረጋገጠ፡፡ ንጉሠ ነገሥቱና ኢትዮጵያዊያንም ከፊታቸው የሚጠብቃቸውን የነፃነት “አዲስ ዘመን” ዜሮ-ዜሮ አንድ (001) ብለው ጀመሩ፡፡

Monday, May 13, 2013

የኢህአፓ (ዴሞክራሲያዊ) ድጋፍ መግለጫ ለተጠራው የሰላማዊ ሰልፍ


 

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)
Ethiopian People’s Revolutionary Party (EPRP ዴሞክራሲያዊ/Democratic)
ግንቦት ፫ ቀን ፪ ሺህ ፭ ዓ. ም
የኢትዮጵያ ሕዝብ የተነጠቀውን መብቱን በትግሉ ይቀዳጀው!
የኢትዮጵያ ሕዝብ አንገብጋቢ የፖለቲካዊ፣ የኢኮኖሚያዊና የማኅበራዊ ጥያቄዎቹን ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ. ም አዲስ አበባ ውስጥ በሰላማዊ ሰልፍ በአንድ ድምፅ ለማሰማት መነሳሳቱን የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ዴሞክራሲያዊ) ከልብ ይደግፋል።Ethiopian People's Revolutionary Party (EPRP Democratic)
በሰማያዊ ፓርቲ የተጠራውን ሰልፍ የምንደግፈው አንገብጋቢ የሕዝብ ጥያቄዎች የችግሮቹ ሰለባ በሆነው ሕዝብ በራሱ በአደባባይ በግልጽና በአንድነት በሰላማዊ መንገድና በይፋም ስለሚገለጹ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ በገዥው አምባገነናዊ ቡድን መብቱንና ሰላሙን አጥቷል። ሕዝቡ ሰላም የሚያገኘው፣ ክብሩንና መብቱን ሊያስመልስ የሚችለው፣ በተባበረ ትግሉ ብቻ ነውና የተደራጁ ኃይሎች በሙሉ ከጎኑ ሊቆሙ ይገባል እንላለን። ሕዝቡ አምባገነኑን ገዥ ኃይል “የተቃውሞ ሰልፍ እንድናደርግ ፍቀድልን!” ብሎ ሲጠይቅ የሚጠበቀው የእምቢታ ምላሽ ሲመጣ ሳይደናገጥ የተነጠቀውን መብቱን፣ በሰልፍ ጭምር ሃሳቡን በነፃ የመግለጽ መብቱ የራሱ ነውና ዛሬም ሊጠቀምበት ይገባል እንላለን።

Saturday, May 11, 2013

የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የመውጣት መብቶች




በሥራ ላይ አለ የሚባለው በ1987 ዓ.ም. የወጣው ሕገ መንግሥት አንቀጽ 30ና 31 የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት፣ የመደራጀት መብት ይደነግጋሉ፤ ነገር ግን ሁለቱም አንቀጾች ግን እያሉ መፍረሻውን ወይም ማርከሻውን አብረው ይገልጻሉ፤ እንዳያማህ ጥራው እንዳይበላ ግፋው ነው፡ይህ ዘዴ በአጼ ኃይለ ሥላሴም ሆነ በደርግ ሕገ መንግሥቶች ውስጥ የሚታይ ነበር፡፡
Prof. Mesfin Woldemariam
የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የመውጣት መብቶች የሕዝቡን ስሜትና ፈቃድ ለማወቅ ለሚፈልግ መንግሥት የእነዚህ መብቶች በተግባር መዋል በጣም ፈላጊ ነው፤ ምክንያቱም መንግሥትንና ሕዝብን ያቀራርባሉ፤ የእነዚህ መብቶች መታፈን የሚያሳየው በመንግሥት ፋንታ አገዛዝ መኖሩንና ሕዝቡን ያለፈቃዱ በኃይል ብቻ የሚገዛ መሆኑን ነው፡፡
አንቀጽ 30‹‹ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፤›› ከአለ በኋላ ‹‹ዴሞክራሲያዊ መብቶችንና የሕዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱ ለማስጠበቅ አግባብ ያላቸው ሥርዓቶች ሊደነገጉ ይችላሉ፤›› በማለት የአንቀጹን ዋና ርእስ ያደበዝዘዋል፤ ያውም ምንም ትርጉም በሌለው ማመካኛ ነው፤ እግዚአብሔር ያሳያችሁ መሠረታዊ የሆነ የዴሞክራሲ ማሙያዎች የሆኑትን የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍን የማድረግ መብት ‹‹ዴሞክራሲያዊ መብቶችንና የሕዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱ›› በሚል በተምታታና ግልጽ ባልሆነ አስተሳሰብ ዋናውን መብት ለመገደብ ‹‹ሕጋዊ›› የሚመስል ማመካኛ ፈጠሩ፤ በዚህም ምክንያት በሕገ መንግሥቱ የተደነገጉ የሚመስሉት አንቀጾች በተግባር ታግተዋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመሰብሰብም ሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ መትረየስንና ክላሽን የሚጋርድና የሚከላከል ጥላ ያስፈልጋል፤ አነዚህ የሕገ መንግሥቱ አንቀጾች ከሥራ ውጭ በመሆናቸው የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበርና የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ወደአለመኖር ተሸጋግረዋል፡፡