Wednesday, April 23, 2014

ካልገደሉ አያቆሙንም – ሃብታሙ አያሌዉ (የአንድነት አመራር) ሰልፉን በተመለከተ

ካልገደሉ አያቆሙንም  (የአንድነት አመራር) ሰልፉን በተመለከተ

ሀገር የመገንጠል ዓላማ ይዞ የተነሳው የህወሓት ጁንታ፣ በስውር እና በአደባባይ የጫካ ልማዱን መሰረት አድርጎ ሲገድል መኖሩ አዲስ


ባይሆንም፣ ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝቼ ነበር፡፡ የመገኘቴ ዓላማም የፊታችን እሁድ 

ሚያዚያ 26 የሚደረገውን

ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የዕውቅና ደብዳቤውን ለመስጠት የተያዘውን ቀጠሮ በማክበር ነበር፡፡
የሰላማዊ ሰልፍ እውቅናን በተመለከተ ኃላፊ የሆኑት አቶ ማርቆስ ፎርም እንዲሞላ አዘዙ፤ የተባለውን ፎርም ሞላን፤ ያን ጊዜ የአቶ




ማርቆስ የቢሮ ስልክ አንቃጨለ፤ አነሱት ......ቀጭን ትዕዛዝ ከወዲያ ማዶ...............
‹‹የአንድነትን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ ዕውቅናው እንዳይሰጥ ይቆይ›› አቶ ማርቆስ ፊቱ ተለዋወጠ ‹‹ ይቅርታ አድርግልኝ የኔ ችግር
አይደለም›› ሌላ ቃል ካፉ አልወጣም፡፡


«አልገባኝም ....ቀጠልኩ ....የአንድነት ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ እያልከኝ ነው ? » መለሰ .....«እኔ ምን ላድርግ ? .....»
«የከለከለው
ማነው የበላይ ኃላፊ ነው ? »
«አዎ»
አጭር መልስ፡፡

ትቼው ወደ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊው አመራሁ፤ ስብሰባ ላይ ናቸው፡፡ ወደ ፓርቲ ጽ/ቤት ደውዬ ሁኔታውን አሳወኩ። የፓርቲው ፕሬዘዳንት ኢንጅነር ግዛቸውን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ፈጥነው ደረሱ፡፡ የአስተዳደሩ ስብሰባም ለሻይ እረፍት ተቋርጦ ኃላፊው ወደ ቢሯቸው ሲገቡ ተከታትለን ገባን፡፡ ላለማናገር ጥቂት አንገራገሩ ። የቢሯቸውን በር አንቀን አናግሩን በማለት ጸናን፡፡

‹‹ምንድነው ችግሩ የሰልፉ ጉዳይ ከሆነ ጨርሰናል፤ እውቅናውን ወሰዳችሁ አይደለም ? ›› አሉ።
ባጭሩ መልስ ተሰጣቸው ፤
«አልወሰድንም ። የአቶ ማርቆስ መልስ ተከልክሏል የሚል ነው፡፡ »
ጥያቄ አስከተልን ......«እርሰዎ መረጃ የለዎትም ? መንግስታዊ ኃላፊነቱ የርስዎ ነው፤ ማነው ከልካዩና ፈቃጁ ? »
መልስ የለም ። ጥቂት ዝም ብለው ‹‹የጠየቃችሁን ሚያዚያ 19 ለማድረግ ነበር፡፡ በዚያ ቀን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የጥበቃ እጥረት አለብኝ በማለት ስላመለከተ የእናንተ ሰልፍ ለሚያዚያ 26 እንዲደረግ ጠየቅናችሁ ። ተስማማን ከዚህ ውጪ የተደረገ ነገር ካለ በኔ በኩል መረጃ የለኝም። ማን እንደከለከለ አናውቅም››

« ስለዚህ ይህንን ከተማ ከንቲባው ካልሆነ ማን ነው የሚመራው? »
ከወዲያ ማዶ መልስ የለም..........ስልክ አነሱ እና አቶ ማርቆስን ወደ ቢሯቸው ጠሩ ። ሰውዬው መጡ ። ማጣሪያ ተጠየቁ። «መመሪያ ደርሶኛል» ሲሉ ለከንቲባው ጽ/ቤት ኃላፊ በኛው ፊት ተናገሩ፡፡ «መመሪያ ሰጪው ማነው?» ወደ አንዱ ቢሮ ዘው ብለን አንድ ሰው አናገርን ...........

‹‹እባካችሁ ይቅርባችሁ ደህንነቶቹ የሚውሉት እዚህ ግቢ ነው፡፡ አንድነቶች ከወጡ እርምጃ ይወሰድ ሲሉ ሰምቻለሁ›› አለን በማንሾካሾክ ድምጽ .............
ጎበዝ ይሙት ሰነፍ ይኑር ቢሻው
አተላ መሸከም ይችላል ትከሻው........... ፍርሃት ማነው ቢሉኝ ስሙን አላውቀውም
 ካልገደሉ አያቆሙንም ሃብታሙ አያሌዉ (የአንድነት አመራር) ሰልፉን በተመለከተ   ሞትን በቁሜ እንጂ ሞቼ አልጠብቀውም፡፡
....................ህወሓት ሊተኩስ ተዘጋጅቷል እኛም የነሱን ጥይት የሚሸከም ደረት .......እመነኝ ካልገደሉ አያቆሙንም፡፡፡ 

No comments:

Post a Comment