Saturday, July 19, 2014

ለዴሞክራሲ ነፃነት በሚደረግ ትግል የሚሸበረው ማን ነው?!

መግቢያ፦ በሜዳ የሚደረገው ትግል እየጠነከረ ሲሄድና ዳሩ መሃል እየሆነ ሲመጣ ነገሮች ሁሉ አዳጋች ሲሆኑ ገዥዎች በሥልጣን ለመሰንበት የሚወስዷቸውን እርምጃዎች ከዚህ ቀደም ደርግ ይወስድ ከነበረው ርምጃ በቂ ትምህርት አግኝተናል። በጭፍን አስተሳሰብ ዐይኑ ያልወደደውን ሁሉ ወደ እስር ማጋዝና ነጻ ርምጃ በሚል ፈሊጥ በጅምላ ሕዝብ ጨፍጭፏል። «የፍየል ወጠጤ ልቡ ያበጠበት»ሳይባል የተገደሉትን ብርቅየ የኢትዮጵያ ልጆችማ ቤት ይቁጠራቸው።


ህወሃት አሁን የሚገኘበት ደረጃ የሚያሳየውም ያነውኑ ነው። በሰላማዊ መንገድ መታገል በራሱ በህወሃት ሕግ የተፈቀደ ነበር። ነገር ግን አንዲት ጠጠር ሳይወረውሩና ቅጠል ሳይበጥሱ ሕጉ በሚፈቅድላቸው መንገድ በመሄድ እየታገሉ ባሉ የተቃዋሚ ኃይሎች ላይ ህወሃት ያደረሰባቸውን እንግልት እስራትና ንብረት ዘረፋ ተመልክተናል። በአብዛኛው እኔ በመጣሁበት መንገድ ካልመጣችሁ በማለት ገፊ ሁኔታዎችን እየተነኮሰም ነው። የሰላማዊ ትግሉን እንዳይቻል አድርጐታል እንጅ ቢቻል በሰላማዊ መንገድ ታግሎ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ ሥልጣን መረከብ ወይም ማስረከብ የ21ኛው መቶ ዓመት ሥልጡን ህዝብ ጨዋ ሥነ-ምግባር ነበር። እነዚህ የኛ ድናቁርቶች ግን በሕገ-አራዊት እየተመሩ ነገር የሚገባቸው ሆነው አልተገኙም።

ሀገር የኮምፒዩተር ቫይረስና ሀከር ነው እንዴ?

ከዓመታት በፊት የቅንጅት አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት አባሎችና ሌሎች ሰዎች ተከሰው ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ”የቅንጅት አመራሮች የፍርድ ቤት ውሎ” በሚል ርዕስ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ተከታታይ ዘገባ አቀርብ ስለነበር ችሎቱ እስኪጠናቀቅ አንድም ቀን ከፍርድ ቤት ቀርቼ አላውቅም ነበር። በዚህም የተነሳ ክሱና የክርክር ሂደቱ ምን እንደሚመስል መናገር የሚያስችል መረጃ አለኝ ለማለት እደፍራለሁ።

በወቅቱ ዐቃቤያነ ሕግ ሽመልስ ከማል፣ አብርሃም ተጠምቀና ሚካኤል ተክሉ (እንዲሁም በስነ ምግባር ጉድለት ከዳኝነት ተባሮ ዐቃቤ ሕግ የኾነ ሰኢድ መሐመድ የተባለ ዐቃቤ ሕግ ነበር በኋላ መምጣት አቆመ) ”ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስና ሀገሪቱን ለማተራመስና ለማናወጥ ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል” የሚል የሀገር ክህደት ክስ ይዘው ፍርድ ቤት ሲቀርቡ የክስ ቻርጁ ይዘትና የተጠቀሱት አንቀፆች የሞት ፍርድን ጭምር የያዙ ስለነበሩ ለማሰብ የሚከብዱ እጅግ አስፈሪ ነበሩ።

የሰማያዊ ፓርቲዋ ወጣት ወይንሸት ሞላ ተፈንክታ፣ እጆቿ በፋሻ ጠቅልሎ፣ ሰውነቷ ዝሎ ፍርድ ቤት ቀረበች




በትናንትናው እለት የአንዋር መስጊድ አካባቢ የሕወሓት አስተዳደር በንጹሃን የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ አሰቃቂ እርምጃ እየወሰደ በሚገኝበት ወቅት መርካቶ አካባቢ ለሥራ ጉዳይ ሄዳ የነበረችው የሰማያዊ ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤትና የሴቶች ጉዳይ አባል ወጣት ወይንሸት ሞላ በደህነንቶች ታፍና ከተወሰደች በኋላ ከፍተኛ ድብደባ ሲፈጸምባት ቆይቶ በዝግ ችሎት ቀርባ 14 ቀን የምርመራ ቀጠሮ ተጠየቀባት።


Friday, July 18, 2014

የዞን 9 ጦማሪያን አባላት “ በወያኔ የስለላ ተቋም ተደርሶበት የተከሰሱበት ማስረጃ” እጃችን ውስጥ ገባ!!


የዞን 9 ጦማሪያን አባላት “ በወያኔ የስለላ ተቋም ተደርሶበት የተከሰሱበት ማስረጃ”  እጃችን ውስጥ ገባ!!

የዞን 9 ጦማሪያን አባላት በወያኔ የስለላ ተቋም ተደርሶበት የተከሰሱበት ማስረጃ”  እጃችን ውስጥ ገባ!! 

ጁምዓ በፖሊስ ጥቁር ሽብር ተናወጠ

ኢ.ኤም.ኤፍ) ዛሬ አርብ ጁምዓ ነበር። የረመዳን ጾም እንደመሆኑ መጠን፤ ለስግደት በጣም ብዙ ሺህ ህዝብ ወደ ታላቁ አንዋር መስጊድ ሄዷል። ከኢህአዴግ ጋር ተመሳጥረው ሙስሊም ወንድሞቻቸውን አሳልፈው በሰጡ እና የ”ኮሚቴ አባሎች” ይፈቱ በሚሉ ሰላማዊ ሙስሊሞች መካከል የተፈጠረው ውጥረት አሁንም እንዳለ ነው። ኢህአዴግ መራሹ መንግስትም ይህን የመከፋፈል አጋጣሚ በመጠቀም፤ “ድምጻችን ይሰማ” የሚሉ ወገኖችን በመደብደብ እና በማሰር መፍትሄ ለማግኘት የሚያደርገውን ጥረት ቀጥሏል።

addis police5
ሹመኛ የመጅሊስ አመራሮችን ዛሬ በይፋ ህዝብ አውርዷቸዋል!!
ይህ አይነቱ በጨለምተኝነት ላይ የተመሰረተ የኢህአዴግ ድርጊት፤ በህዝብ ላይ የሚተገበር “ጥቁር ሽብር” ከማለት ውጪ ሌላ ትርጉም የሚሰጠው አይደለም። ለዚህም ነው በርእሳችን ላይ “ጁምዓ በፖሊስ ጥቁር ሽብር ተናወጠ” ያልነው።  ይህ ሽብር እና ነውጥ ምን ይመስል እንደነበር የበለጠ ለመረዳት በስፍራው ተገኝተው፤ የአይን ምስክር ሆነው ዘገባቸውን ያቀረቡትን የጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና የጌታቸው ሽፈራውን ዜና መመልከት በቂ ነው። በቅድሚያ ጋዜጠኛ ኤልያስን ዘገባ እናስቀድማለን።

Thursday, July 17, 2014

እስረኞቹ በሽብር መከሰሳቸውን አያውቁም

ከእስሩም በላይ - “ሽብርተኝነት”

 
 
 ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ
tsiongir@gmail.com


አንድ ዓመት ከአንድ ወር ኾኖታል። እስክንድር ነጋ ከታሰረ ከዐስራ ስምንት ወራት በኋላ ከባለቤቱ ከጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል እና ከልጁ ከናፍቆት በተጨማሪ ለመጀመሪያ ጊዜ ሌላ ሰው እንዲጠይቀው በሰኔ የመጀመሪያ ወር ላይ በ2005 ዓ.ም. እንደተፈቀደለት ነው። በወቅቱም እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ወደሚገኘው እስር ቤት አምርቼ ነበር።

ተገናኝተን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላም እንዲህ አለኝ፤”ሽብርተኛ አይደለኹም፤ሀገሬ በማንም እንድትሸበር አልፈልግም አልፈቅድምም እኔ የምፈልገው የሀገሬ ሕዝቦች በነጻነት የሚያስቡባትና የሚንቀሳቀሱባት ሰላማዊ ሀገር እንድትኾን ነው”፤እስክንድር ”ሽብርተኛ” አይደለምና ከእስሩም በላይ ያንገበገበው ”አሸባሪ” መባሉ ነበር።

እስክንድር ”ጋዜጠኛ” ነው። እስክንድር ሲጽፍ ሀገሪቱ ላወጣችው ሕግ ራሱን አስገዝቶ፣በሀገሪቱ ሕግ ማዕቀፍ ሥር ራሱን ገድቦ ነው። ይህም ኾኖ ግን ሲጽፍ ሕግ ተጥሶ አደጋ ሊደርስበት እንደሚችል፣ሲጽፍ ሕግ ተጥሶ ሊታሰር እንደሚችል ያውቃል። ግን ደግሞ ቢታሰር በቀጫጭን መስመርም ቢኾን በሀገሪቱ ሕግ ተዳኝቶ ከእስር ሊለቀቅ እንደሚችል ያምን ነበር።በዚህ እምነቱም የመጣበትን ለመቀበል ተዘጋጅቶ ሀገሩ ላይ ቁጭ ብሎ ይጽ

ከመጻፍ እና ሐሳቡን በአደባባይ ከመግለጽ ውጭ ያሉት መንገዶች እስክንድርን አይመቹትም። እስክንድር ሐቀኛና ቀጥተኛ የኾነ አስተሳሰብ ያለው ላመነበት ነገር የታመነ ንጹህ ኢትዮጵያዊ ነው። ምናልባት ይህን ”እስክንድርን” ለመረዳት እስክንድርን ማወቅ ሊጠይቅ ይችላል። እስክንድርን ያኔ ቃሊቲ ሳገኘው ሽብርተኛ አለመኾኑን ደጋግሞ ነገረኝ። 

የፖለቲከኞቹ እስር እና ያስከተለው ሕገመንግሥታዊ ጥያቄ





ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ጋር ሰሞኑን ባደረጉት ቃለምልልስ የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከየመን ወደኢትዮጵያ ተላልፈው የመሰጠታቸው ጉዳይ በማንሳት “የኢትዮጵያ መንግስት የፖለቲካ ፓርቲዎችን ሽፋንአድርጎ የሚመጣአሸባሪነትንአይታገስም”ማለታቸውን ዘግቧል።
     
የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን መያዝ ተከትሎ በሀገር ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት መካከል አቶ ሐብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከአንድነት፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ ከሰማያዊ ፓርቲ፣ አቶ አብርሃ ደስታ ከአረና ትግራይ (ዘግይቶም ቢሆን ፍ/ቤት ቀርቧል)፣ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወሳል። የጸረ ሽብር ግብረሃይል የግንቦት 7 ልሳን ከሆነው ኢሳት ቴሌቪዥን ጋር ግንኙነት ያላቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በቁጥጥር ስር ማድረጉን በደፈናው በዕለቱ የገለጸ ሲሆን የተያዙት የአንድነት፣ የሰማያዊና የአረና አመራሮች መሆናቸው ሲታይ መግለጫው እነሱን በቀጥታ የሚመለከት ስለመሆኑ የብዙዎች ግምት ሆኗል።

እስሩ እና የፓርቲዎች ምላሽ