Wednesday, March 20, 2013

ያ ትውልድ ይመስክር



                                                       
                                                           እራሱን ቢያመጣ ታሪክ ተመልሶ

                                                           ዛሬም አለሁ ቢለን የትናንቱን ጥሶ

                                                           ያሳየን ይሆን ወይ የዚያን ዘመን ትውልድ

                                                            እንደ ሻማ ቀልጦ ለሌላው የሚነድ

                                                                 
                                                                    ያ ትውልድ ! ለጠላት ዓላማ ያላጎበደደ

                                                                   ታሪክን ያልናደ እውነትን ያልካደ

                                                                   ግንባሩን ሳያጥፍ ከጠላት ተናንቆ

                                                                    ስንቱን አፈር በላው ስንቱ ቀረ ወድቆ ፤

                                                                     በደሙ ጠብታ በአጥንቱ ክስካሽ

                                                                     ተጠየቅ ለሚሉት እየሰጠ ምላሽ

                                                                      አለፈ ያ ትውልድ ላናየው ዳግመኛ

                                                                      ያደራ ቃል ትቶ፡ አስረክቦ ለኛ ፤

ቋንቋ የሕወሃት የጥፋት ሚዛን እና የመጭው ዘመን የኢትዮጵያዊያን ስጋት



ልቃቂት ነው ሂዎት፤ በእንዝርት ላይ እንደሚሽከረከረው የጥጥ ንድፍ ዘለላ እየተጠማዘዘ እየተሽመለመለ፣ እየጠበቀና እየላላ፣ እየተወጠረና እየረገበ የሚጠመጠም የሂዎት አንጓ። ያንዱ ሂዎት ዘርፍ በሌላው መሰረት ላይ እየተመጠነና እየተደረበ የሚከወን ኩነት። የስረኛው የላይኛውን ተሸክሞ፣ የላይኛውም በስረኛው ላይ ያለጭንቀት ተመቻችቶና ተንደላቆ የሚቀመጥበት ልቃቂት ነው ሂዎት። ደግሞም እንደ ታሪክ የሚመዘዝ፣ የሚተረክ እንደ ልቃቂት የፈትሉን ጫፍ ይዘው የሚተረትሩት የሚያወጉት፤ ክፉ ደጉን፣ ሳቅ ዋይታውን፣ የጀግንነት የፍቅር ወጉን፣ ያንን ዘመን ያን የጥንቱን፣ የነንቶኔን የነንቶኔን፣ ምርቃቱን ቱፍቱፍታውን፣ የልጅነት ያፍላነቱን፣ የሚያሳየን የሚያሞቀን፣ ወዲያው ደግሞ የሚያበርደን፣ አበሳጭቶ የሚያነደን፣ አስደስቶ የሚያነጥረን፣ ያው ሂዎት ነው ልቃቂቱ፣ የጥንት ያሁን ወደፊቱ፣ እናም እንዲህ እንዲህ ብሎ፣ ስቃያችን አበሳችን ፉከራችን በያይነቱ ተጠቅልሎ፣ አሁን እኛ ከለንበት እኔ ዛሬ ከማወራው፣ ታሪክ አንጓ እንኳ ለመድረስ 68 ዓመት ሞላው። ይችን ትንሽ የታሪክ ጫፍ፣ ይዘን ሽምጥ ስንከንፍ፣ ልክ ከ68 ዓመት ደጃፍ፣ ሆሎኮስት ነው የሚገዝፍ። ከምስራቅ ጫፍ ጃፓን ጠረፍ፣ እስከ አሜሪካ ዳር ድንበር ጽንፍ፣ ከሩሲያ ጀርመን ጓዳ፣ ሳውዝ አፍሪካ ድረስ የፈነዳ፣ የዓለምን ቅስም የሰበረ፣ ያማረረ ያሳረረ፣ አውራ ኩነት እኩይ ተግባር ይህ ነበረ። እኔም እንግዲህ ዛሬ፣ ከታሪክ አንጓ ቆንጥሬ፣ ከሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር እየቃኘሁ፣ ዝግጅቴን ያው ለእናንተ ብያለሁ።
ኩነቱ ከአንደኛው የዓለም ጦርነት በቅርብ ርቀት የተከወነ ቢሆንም ለወቅቱ ከፍተኛ የሚባል ዝግጅት ተደርጎበታል። ዓለምን በሁለት ጎራ አቧድኖ አቆራቁሷል አፋጅቷልም። እስከ አሁንም ድረስ ለማሰብ የሚያዳግቱ፣ ለማስታወስ የሚዘገንኑ፣ ለማየት የሚቀፉ በፍርሃት የሚያርዱ ድርጊቶች ተከውኖበታል። በወቅቱ የወደመውን ንብረት የጠፋውን ሃብት መጠን ለጊዜው እንተወውና ስድስት ሚሊዮን አውሮፓዊያን ይሁዲዎችን ጨምሮ ካስራ አንድ ሚሊዮን በላይ ንጹሃን ዜጎች ሂዎታቸውን ገብረውበታል- ሆሎኮስት ሁለተኛው የዓለም ጦርነት።

የኢህአዴግ አፋኝ አስተዳደር የአፓርታይድ ቅርጽ እየያዘ ነው!



ሰማያዊ ፓርቲ
ዛሬ መጋቢት ስምንት ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽነት ማህበር፤ ሰማያዊ ፓርቲ እና ባለራዕ ወጣቶች ማህበር በጋራ በመሆን “ለፋሽስቱ የጦር ወንጀለኛ ለማርሻል ግራዚያኒ ክብር መስጠት የአባቶቻችን መስዋዕትነት ማራከስ ነው” በሚል የተጠራውን ሰልፍ አምባገኑ የኢህአዴግ መንግስት በርካታ የፌደራል ፖሊስ፣ የደህንነት አባላትን እና የአዲስ አበባ ፖሊሶችን በማሰማራት ሲበትን፤ የተቋማቱን ከፍተኛ አመራሮች፤ ታዋቂ ግለሰቦች እና በርካታ ወጣቶች ጨምሮ ቢያንስ 34 ሰዎች አስሯል የታሳሪዎች ቁጥር አሁንም በመጨመር ላይ ነው፡፡የኢህአዴግ አፋኝ አስተዳደር የአፓርታይድ ቅርጽ እየያዘ ነው!
እንዲሁም በትላንትናው እለት ለተቃውሞ ሰልፉ የቅስቀሳ ስራ ሲሰሩ ከነበሩት ውስጥ 2 የሰማያዊ ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ አባላትን እንዲሁም የባለራዕይ ወጣቶች የስራ አስፈጻሚ አባላትን ጨምሮ 8 ሰዎችን አስረዋል፡፡
በአሁኑ ሰአት በእስር ላይ የሚገኙት እና ስማቸው የተገኘ
1. ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም
2. አቶ ታዲዎስ ታንቱ
3. አቶ ይልቃል ጌትነት (የሰማያዊ ሊቀመንበር)
4. ስለሺ ፈይሳ (የሰማያዊ ም/ሊቀመንበር)
5. ይድነቃቸው ከበደ (የሰማያዊ የህግ ጉዳይ ሀላፊ)
6. ሀና ዋለልኝ (የሰማያዊ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊ)
7. ጌታነህ ባልቻ (የሰማያዊ የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ)
8. ብርሀኑ ተክለያሬድ (የባለራዕይ ወጣቶች ተ/ምክትል ሊቀመንበር)
9. ያሬድ አማረ (የባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ጸሀፊ)
10. ኤልሳቤጥ ወሰኔ

Sunday, March 17, 2013

ሰንሰለቱም ይጠብቃል፤ እርግጫውም ይከፋል …ካልተነሳን!




አስተዳደር በየፈርጁና በየደረጃው፤ ከብሄራዊ መንግስት እስከ ታች የቀበሌ አመራር በመጥፎም ይሁን በደግ መልኩ በዜጎች ህይወት የለት ተለት እንቅስቃሴና አኗኗር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ እንደሚኖረው ሁሉም ሰው እየኖረው ስለሚያየው ማስረጃ መደርደር ላያስፍልገው ይችላል።
በሀገርና በህዝባዊ ጉዳዮች ውሳኔ አሰጣጥ ላይ እናም ውሳኔውን በማስፈጸም ሂደት ላይ ዋናው ተዋናይ በመንግስትነት የተሰየመው አካል ሲሆን፤ እንደየ ሀይላቸውና ቅቡልነታቸው፤ በመንግስት ውሳኔ ላይ ተጽእኖ ማሳደር የሚችሉ ወገኖች መኖራቸው የተለመደ ነው። ለምሳሌ የፖለቲካ ድርጅቶች፤ የሰራተኛ ማህበራት፤ የገበሬ ማህበራት፤ የሙያ ማህበራት፤ ተደማጭ ግለሰቦች እናም አለም አቀፍ ሀይላት፤ የመገናኛ ብዙሀን፤ የገንዘብ ተቋማት፤ ወዘት……ከሁሉም  በላይ ደግሞ ሕዝብ!!..ዲሞክራሲ ባለበት ሀገር ውስጥ በመንግስት ውሳኔ ላይ ተጽእኖ ማሳደር ይችላሉ።
ወደእኛ ሀገር ጉድ የመጣን እንደሆነ በተለይም በደርግና በዘረኛው የወያኔ አስተዳደር ዘመን ፍጹም በሆነ ወደር ያልተገኘለት አንባገነንነት ስር በመውደቃችን፤ የምንታገልለትና የምንመኘው ዲሞክራሲ ጭላንጭሉም እስከወዲያኛው በመጥፋቱ፤ እንኳን የፖለቲካ ድርጅት፤ እንኳን የሙያ ማህበር፤ ህዝብ በነቂስ ከቤቱ ወጥቶ አደባባይ ውሎ አድሮ አቤቱታ፤ሮሮም ሆነ ተቃውሞ ቢያሰማ ወያኔ ከጥፋት አቋሙ ፍንክች እንደማይል ለኢትዮጵያ ህዝብ በተግባር አሳይቷል። ሙስሊም ወንድሞቻችን ከአመት በላይ በሰላም እየታገሉለት ያለው የሀይማኖት ነጻነት ምላሽ ማግኘት ቀርቶ ጭራሽ ይህን አንገብጋቢ ህዝባዊ ሰብአዊ ጥያቄ ወደ ወንጀልነት ቀይሮ፤ ንጹሀን ዜጎችን ወህኒ መቀመቅ ለማጎር ወያኔ የሚያደርገውን ሩጫ እየተመለከትን ነው አዲስ ነገር ባይሆንም።

Tuesday, March 12, 2013

እኛና እነሱ – የሁለት ሀገር ሰዎች ነን


እም! ብዬ እያማጥኩ ጀመርኩት።
eprdf leanders in ethiopia
(ፎቶ – ከኢትዮጵያ ከረንት አፊርስ ዲስከሽን ፎረም የተወሰደ)
እኛ ማነን? እኛ የተቀመምንበት ኢትዮጵያዊነት የሚያንገበግበን። ችግሯ – ችግራችን፤ ዕንባዋ – ዕንባችን፤ መከፈቷ – መከፈታችን፤ ጉስቁልናዋ – ጉስቁልናችን፤ አንገት መድፋቷ ሃዘናችን የሆነው በዬትኛውም ዓለም የምንገኝ ልጆቿ ነን። በወያኔ መዳፍ ውስጥ አሳሩን በማዬት የሚገኘው ከስሜን እስከ ደቡብ ጫፍ፤ – ከዱቡብ ጫፍ እስከ ምዕራብ ጫፍ፤ ከምዕራብ ጫፍ እስከ ምስራቅ ጫፍ የሚገኝ ህዝብ ለሀገሩ ልዩ መለዮችን የሆነው ሥጋና ደም ነን።
እነሱስ? „የደላው ገንፎ ያላምጣል“ እንዲሉ ከማህደረ – ኢትዮጵያዊነት ትንሽ ልቅላቂ ያልፈጠረላቸው፤ አለቶች … በዕንባ ላይ ይሾማሉ፤ ይሸለማሉ …. ልጆቻቸውን አንደላቅው ያሰተምራሉ፤ ሲሰኛቸው ውጬ ልከው ዶላር አፍሰው ያዝመነምናሉ።
ባይታዋሩ ወገናችን ደግሞ ዕጣ ፈንታው … ሥራ ፍለጋ በሺህዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን፤ በውሃ ጥም፤ በመንገድ ጉዞ አቅም በማነስ፤ በውሃ ሙላት፤ በጾታ ጥቃት፤ በቀጣሪ ዳባ እንደተበተነ ያልቃል፤ እንዲሁም ካሰቡት ሳይደርሱ የአሞራ እራት ይሆናል። በስደቱ በእሳት የሚቀቀሉት፤ ከፎቅ ተከስከስሰው የሚሞቱት፤ በጭንቀት በሽታ አብደው አድራሻቸው ጠፍቶ የሚቀሩትንማ ስሌትም አይገታውም። እንደ ጣሊያን በመሳሰሉት ሀገሮችም መንገድ ላይ ተዳዳሪ ወገኖቻችን በሚመለከት — ቤቱ ይቁጠረው።

ለኢትዮጵያ እንድረስላት ይህን ሳናደርግ የቀረን እንደሆነ ግን ህሊና ቢስ ነን ፍሬ ቢስ ነን ወይም ደግሞ ከሃዲ ነን



በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁናቴ ህዝቡ ዕድሉን አግኝቶ ወደውጭ የወጣ እንደሆነ ወደ ዓገር ቤት ተመልሶ ቢገባ የጭንቅላት በሽተኛ ወይም እንደ እብድ አልያም እንደ ሞተ
autor yared elias Brehane

ሰው ተቆጥሮ የህድር ጡሩንባ ተለፍፎ ዘመድ አዝማድ ተሰባስቦ የሚላቀስበት አልያም ደግሞ ከቤተሰብ ትዳር አንስቶ የሰፈር ሰው ትንሽ ትልቁ የስራ ባልደረባ ከታክሲ ሹፌር እስከ ዶክተር እስከ ትልቁ የወያኔ አገዛዝ ሚኒስቴር ድረስ እንደዘመኑ በሽታ ታይቶ የምትገለልበት ወሬው ሁሉ እንትና ደቡብ አፍሪካ ጠፋ በሞያሌ በሱዳን ሊቢያ  እየተባለ ስንቱ  ተስፋ ቆርጦ የሱሰኛ ተገዢ የሚደረግበትዘመን። ሌላው ይቅርና  እትብቱ ወደተቀበረበት ሃገር ለመመለስ እንኳን የወያኔ ገዢ ፓርቲ 10 ግዜ እንድናስብ የሚነግረን ወቅት  እንደነገሩ ተበልቶ አንዲት ለስላሳ ለመጠጣት 20 ግዜ የሚታሰብበት ቢራ ለመጠጣት ዱቤ ለመጠየቅ 40 ግዜ የሚታሰብበት ሃገር።  ስለ እውነት ስለነጻነት ቢጠየቅ ደግሞ ምን ሊሆን እንደሚችል መልሱን ? ..ለነሱ………የሚባለበት ግዜ ።
መቼስ አገሩ ላይ መኖር የሚጠላ ስው ያለ አይመስለኝም ግና ገና አካሉ አገሩ ላይ ቍጭ ብሎ መንፈሱ ውጭ አገር ያለውን ስንቱ ይቍጠረው። በውጭ ሃገር የሚኖረውማ  ወደ ሃገሩ ተመልሶ ሃገሩ ላይ ሃገሩን ወገኑን ለማገልገል የፈለገ ሰው ሃገሪቷ ላይ መኖር የማይችልበትን የጥቂት ዘረኛ ወያኔ አገዛዝ መንግስት የሚኖርባት በመሆኑ ለማድረግ አይችልም። በዛ ላይ ሰሞኑን ያየሁት የሰለሞን ቦጋለ እና ሳምሶን ቤቢ ፊልም በጣም ሲከነክነኝ ነው የዋለው አዎ የዚህ ደራሲ በፈለገው መልኩ ይጻፈው እኔ በተረዳውት ግን ለዚያች አገር ለዛ ህብረተሰብ ነጻነት ያስፈልገዋል ። መልዕክቱን በፈለጉት መልኩ ያስተላልፉት ግን በደንብ የሚታይ ነገር ነበረበት ስለነጻነት ብሩህ ተስፋ ።