Wednesday, August 6, 2014

“ስለእኔ አታልቅሱ!”

 ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

“ዋይ ዋይ ከሚሉና ሙሾ ከሚያወጡ ሴቶችና ከሕዝቡ እጅግ ብዙዎች ተከተሉት፡፡ ኢየሱስ ግን ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አለ፡- እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች ለእኔስ አታልቅሱልኝ፤ ዳሩ ግን፡-
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

መካኖችና ያልወለዱ ማኀፀኖች፣ ያላጠቡ ጡቶችም ብፁአን ናቸው የሚሉበት ጊዜ እነሆ ይመጣልና ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ፡፡” (የሉቃስ ወንጌል ም. 23 ቁ. 27-30) ከቅዱስ መጽሐፉ ይህን የመሲሁ የመጨረሻ ምክር የመረጥኩት (ምንም እንኳ ረቢው የተናገረው ስለመለኮታዊው ትምህርት ቢሆንም) ዓለማዊው ፍች የኢትዮጵያችንን የወቅቱን መንፈስ ለመረዳት ከማስቻሉም በዘለለ፤ በየጊዜው እያየን፣ እየሰማን ያለነውን የፖለቲካ ተቃውሞው የጥምዝምዞሽ መንገድ በአርምሞ ለመመርመር መልካም ምሳሌ ይሆናል በሚል እሳቤም ነው፡፡

የአርባ ምንጭ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎች ታሰሩ

ሐምሌ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዞኑ ፖሊሶች ትናንት ከሌሊቱ 10 ሰአት ላይ ወደ ሰማያዊ ፓርቲ የአርባ ምንጭ አመራሮች መኖሪያ ቤት በመሄድ ፍተሻ ካደረጉ በሁዋላ ፣ አመራሮችን ወስደው አስረዋቸዋል።

የፍርድ ቤት ማዘዣ ይዘናል በማለት ፍተሻ ያካሄዱት ፖሊሶች በአንደኛው ቤት ውስጥ ሁለት ፍሬ ጥይቶችን ማግኘታቸውን ሲያስታወቁ፣ በሌሎች መኖሪያ ቤቶች ደግሞ
ቪዲዮ ካሜራዎችን፣ ፊልሞችንና የተለያዩ ወረቀቶችን ሰብስበው ወስደዋል። የአንደኛው አመራር የቅርብ ሰው የሆነ ለኢሳት ሲናገር፣ ፖሊሶቹ ጠመንጃ በሌለበት ሁለት
ጥይቶችን አገኘን ማለታቸው አስቂኝ ነው ካለ በሁዋላ፣ ሁለቱንም ጥይቶች ፖሊሶች ራሳቸው ይዘው መምጣታቸውንና አገኘን ብለው መናገራቸውን ገልጿል።

የዋሽንግተኑን የአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤ ኢትዮጵያውያን ተቃወሙት

                                                 
                                                       "ኦባማ ዝምታው ይብቃ"
ኢትዮጵያውንና ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን በዛሬው እለት በዋሽንግተን ዲሲ የተከፈተውንና በዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ከአፍሪቃ መሪዎች ጋር የሚያደርጉትን ጉባኤ በመቃወም አደባባይ ወጥተዋል።

“በኢትዮጵያ የሚታየው የሰብዓዊ መብት ረገጣ እንዲቆም አዎንታዊና ተጨባጭ ግፊት በማድረግ ፋንታ፤ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶቹን አራማጆች በመደገፍ ሁኔታው ይበልጥ እንዲባባስ እያደረገ ነው፤” ሲሉ ከተለያዩ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች የመጡ መሆናቸውን ያስታወቁት የሰልፉ ተሳታፊዎች የኦባማን አስተዳደር ኮንነዋል።

ስብሰባውን አስመልክቶ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ወደ ርዕሰ-ብሔርነቱ በዘለቁ ወቅት ሃገራቸው ከነበረችበት የምጣኔ ኃብት ድቀት አሁን እያገገመች በመሆኗ ትኩረታቸውን ለአፍሪካ እየሰጡ መሆኑን የሚያሳዩ ክንዋኔዎችን እያደረጉ ነው በማለት ቀድሞ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሣደር የነበሩትና የጆርጅ ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር ዴቪድ ሺን መናገራቸውን ያሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ዘግቦ ነበር፡፡

Tuesday, August 5, 2014

የሕወሓት ጄኔራሎች ሲታመሱ ዋሉ ። በሰራዊቱ ውስጥ አለመተማመን ነግሷል።

ምንሊክ ሳልሳዊ


በጥርጣሬ/ግምት ካልሆነ በቀር አስራ አራቱ መኮንኖች የት እንደገቡ አይታወቅም።
ሁለት ከፍተና የጦር መሃንዲስች ዱካቸው ደብረዘይት ከሚገኘው እስር ቤት ተገኝቷል።
ወደ መቀሌ ከዲያስፖራው ጋር ለዘረፋ የንግድ ሽርክና ኢንቨስተሮች ለመመልመል ያመሩት ጄኔራሎች ሳይቀሩ በምን እንደመጡ በማይታወቅበት ሁኔታ አዲስ አበባ ደርሰው የመሃል አገር መኮንኖች መጥፋትን ተከትሎ ያመጣውን ውጥረት በስብሰባ ሲያሹት እና ከተለያዩ ወታደራዊ ደህንነቶች መረጃ ሲሰበስቡ እንደዋሉ ታውቋል።

በሰራዊቱ ውስጥ አለመተማመን የተፈጠረው ከምን የመነጨ ነው የሚል ጥናት በዚህ ሳምንት በተካሄደበት የመሃል አገር መከላከያ መምሪያዎች ውስጥ አጋጣሚ በተገኘ መረጃ 16 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የት እንደገቡ አይታወቅም ሲል ሪፖርት ያቀረበው የወታ
ደራዊ ደህንነት ቡድን የቀረበለትን ጥቆማ ለበላይ አካላት ሪፖርት ሳያድርግ ፍተሻውን አጧጡፎት የነበረ ቢሆንም ምንም አይነት 
ፍንጭ ባለማግኘቱ ትላንትና የተነገረው የበላይ አካል በከፍተኛ ድንጋጤ ተውጦ የዋለ መሆኑን ለጦር ክፍሎቹ ቅርብ የሆኑ ምንጮ
ቻችን ከመከላከያ ያደረሱን መረጃ ጠቁሟል።

ኢህአዴግ በድሆች ጉሮሮ ላይ ቁማር መጫወቱን ቀጥሎበታል፡፡ የደመወዝ ማሻሻያ ርካሽ የፓለቲካ ትርፍና ተግዳሮቱ

ምንሊክ ሳልሳዊ


***የደመወዝ ማሻሻያ ርካሽ የፓለቲካ ትርፍና ተግዳሮቱ….***
በድሆች ጉሮሮ ላይ ፓለቲካውን የሚያካብተው ኢህአዴግ በተቀጣሪዎቹ ላይ ቁማር መጫወቱን ቀጥሎበታል፡፡

ተቀጣሪው የኢትዮጵያ ህዝብም ባርነትን ወዶ መኖሩን ተያይዞታል፤ የሰውን ልጅ ከጫማህ ስር በባርነት ለማኖር ከፈለግክ ቤተሰብ መጦር ድሮ ቀረን እያዜመ በቤተሰብ የሚጦረው የዘመናችን የመንግስት ሠራተኛ አያድርሰው እንጅ ቢታመም ጉድ ፈላ! ያው ጤና አዳሙን፣ዳማከሲዩን፣ዝንጅብሉን አጥር ያፈራውን ሐረግ ሬሳ ይታጠናታል እንጅ እንኳንስ የግል ሆስፒታል በቀበሌው ያለ ጤና ጣቢያ ሔዶ በሐኪም ሊታይ አይችልም፤ በዓመት በዓል እንኳን ከመንግስት ሠራተኛ ቤት የልኳንዳ ፌስታል እንጅ የበግ ቆዳ የገባው በደጉ ዘመን ነበር፤ለመማር እራስን ለመለወጥ ገንዘብ ያስፈልጋል፤ከተማርክ ደግሞ ጥያቄ ማንሳትህ አይቀርም! የዛሬን ካልቸገረህ ስለ ነገህ ትሞግታለህ! ማኩረፊያ ካለህ ምሰህን አስከብረህ ለእራትህም ትተርፋለህ! ቅሉ ግን ከምሳ ባሻገር እንድትኖር አይፈለግም፡፡ ከምሳ ያለፈ እንድታስብ አይፈለግም! ሆድህ ከሞላ ቁንጣንህ ወንበር ያሰይሃል ተብሎ ይታመናል-በኢህአህዴግ ቤት! እራትህን እርግጠኛ ከሆንክ መታረዝህ ያሳስብሃል! ቁርሳቸውን ላላሟሹቱ ማሰብ ትጀምራለህ! ሌሎች መብቶችህም ትውስ ይሉህ ይሆናል! ከራስህ አልፈህ አገሬ ብለህም ትነሳ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ሆድህ ይሞላ ዘንዳ አይፈለግም፡፡ ደንደስህ ከወፈረ ለማነቆ አይመችም! የኢትዮጵያ የተቀጣሪዎች የደመወዝ እስኬል ዝቅተኛ ነው ብለህ ማንሾካሾ አትችልም፤ አደሃሪ ጓደኛህ 
ይቺ አገር ከዚህ በላይ ደመወዝ ለመክፈል አቅሟ አይፈቅድም ብሎ በሐገርህ ፍቅርህ ስስ ጎንህ በኩል ዘልቆ ይሞግትና ዝም ያሰኝሃል!
 አዎ! ይኢ አገር የተትረፈረፈ ደመወዝ መክፈል ያቅታት ይሆናል፤ እነ እንቶኔ ከጓሯቸው እንደ ባህር ዛፍ የሚያበቅሉትን ህንጻ መስሪያ
 የሚያክል ደመወዝ አልተመኘህም! ከእርሀብና ከእርዛት፣ከጥማትና ድቆሳ የሚያላቅቅ ገንዘብ ግን ኢትዮጵያ መክፈል አይሳናትም፤
 ደግሞስ የመሬቷ ኢትዮጵያ ይፋ የምትሆነው ደመወዝ ላይ ብቻ ነው እንዴ? የኢትቪዋ ኢትዮጵያ የት ገባች?

Monday, August 4, 2014

አንድ መቶ ሰባ አምስት ኪሎ ወርቅ ከሃገር ሊወጣ ሲል ቢያዝም በሳሞራ የኑስ ትእዛዝ እንዲያልፍ ተደርጓል።


ምንሊክ ሳልሳዊ

  • 661
    Share
የጄኔራል ሳሞራ የኑስ እንደሆነ የሚጠረጠረው አንድ መቶ ሰባ አምስት ኪሎ ወርቅ ከአገር ሊወጣ ሲል ተይዞ የነበረ ቢሆንም በጄኔራሉ ትእዛዝ ከአገር እንዲወጣ መደረጉን የአየር መንገዱ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል። ይህ በሁለት ካርቶን ታሽጎ በበረራ ቁጥር 600 እና 612 ወደ ዱባይ ሊሻገር ሲል በቁጥጥር ስር የዋለው ወርቅ በጊዜው ባለንብረቱ ተፈልገው ባለመገኘታቸው እንዲቆይ ቢደረግም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ቦታው ድረስ አሽከሮቹን በመላክ እንዲለቀቅ እና እንዲያልፍ/እንዲጫን የተደረገ መሆኑ ታውቋል።

ይህ የሃገር ሃብት የሆነን ወርቅ የወያኔ ባለስልጣናት ካለምንም ገደብ በማሸሽ እና በመዝረፍ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ፒያሳ አከባቢ በሚገኘው በአፍሪካ ወርቅ ቤት ሽፋን እንዳልካቸው እና ዳንኤል በሚባሉ ስሞች በሚሊዮን ዶላሮች የሚገመት የወርቅ መጠን ከአገር በማስወጣት እና እንዲሁም የውጪ ወርቆችን ካለምንም የቀረጥ ክፍያ ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ስራ ላይ መሰማራታቸው በተጨማሪም ሃገሪቷ የምታገኛቸው የውጪ ምንዛሬዎች በጥሬው እየታሸጉ ከሃገር እንደሚወጡ ታውቋል።

Friday, August 1, 2014

የህወሃት ሽብር መቆም አለበት!

ዛሬ በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለ አሸባሪ ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎችን በፖለቲካ አመለካከታቸው፣ መንግስት በመተቸታቸው በግልጽ በመጻፋቸውና በአደባባይ በመናገራቸው ከዚህም አልፎ በጥርጣሬ በተለይም በብሄረሰብ ማንነታቸው እያሳደደ የሚያፍን የሚያሰቃይና የሚገል የሽብር ተቋም ካለ ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ መሬት ላይ ሰላማዊ ዜጎችን ኢላማ ያደረገ የተቃውሞ ሃይል በተግባርም ሆነ በአስተሳሰብ ከወያኔ ውጪ አንዳች ሃይል የለም።
አፋኙ የወያኔ ስርአት በተለየም የህዝቡን ሀብትና ንብረት እየዘረፉ የሚቀማጠሉት የህወሃት መሪዎችና ሎሌዎቻቸው የተቃውሞ ድምጽ በሰሙ ቁጥር እንደሚሸበሩና እንቅልፍ አጥተው እንደሚያድሩ ይታወቃል። አፍነውና ዘርፈው ገለው የሚገዙት ህዝብ ግፍ በዛብኝ ብሎ በተናገረ ቁጥር የሚሸበሩት እነሱ ብቻ እንጂ ህዝቡ አይደለም።