Sunday, April 14, 2013

ዘር ማጥራትን ያህል ወንጀል ፈጽሞ ይቅርታ መጠየቅ ፌዝ ካልሆነ ድራማ ነው


Amhara Ethnic group members Ethiopia
በፌዴራል ስም የተሸፈኑ ህውሃት/ኢህአዴጎች እና በአቶ መለስ ራዕይ የተጠመቁ የክልል ፖለቲከኞች በኢትዮጵያ የዘር ማጥራት (Ethnic Cleansing) ወንጀል ስለመፈጸማቸው መዘገብ ከጀመረ ውሎ አድሯል። ይኽ ዜና በኢትዮጵያ ወዳጆች ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ዜጎች ዘንድ ስጋት ፈጥሯል። ኢትዮጵያ እንድትበተን የሚፈልጉ ግን አፍና እጃቸውን አስተባብረው ኢትዮጵያ የምትባል አገር ከመንገዳቸው ላይ ተወግዳ ህልማቸው ወደሆኑት የቃል-ኪዳን አገሮቻቸው (Promised-land) ለመድረስ የጀመሩትን ጉዞ ፍጥነት እና ግልጽነት ሳያመቻቸው ዝቅ ሲያመቻቸው ደግሞ ከፍ ያደርጋሉ እንጂ አያቆሙም። የህውሃት ሕገ መንግስት (አንቀጽ 39) ግፉ በርቱ ይላል። ስለዚህ የቤንሻንጉል ጉምዝ አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ናስር ቀደም ብሎ በቪኦኤ አማርኛ ፕሮግራም ሲጠየቅ አፉን ሞልቶ ሞቅ ባለ ስሜት አማርኛ ተናጋሪውን ያፈናቀልነው መሬቱን ለልማት ስለፈለግነው ነው እንዳላለ ሁሉ ድንገት ተነስቶ ሰሞኑን ይቅርታ መጠየቁ ማጭበርበሪያ ድራማ እንጂ ሃቅ አይደለም። ይኽ ይቅርታ ከራዕይ እና ከፖሊሲ ለውጥ የመነጨ ሳይሆን የተለመደው የህውሃት ማዘናጊያ እና አቅጣጫ ማስቀሪያ ፕሮፖጋንዳ ነው። ለአንድ ደቂቃ እንኳን መዘናጋት የለብንም። ላብራራ።

Monday, April 8, 2013

የህወሓት/ኢሕአዴግ የዘር ማጽዳትና የዘር ማጥፋት ዘመቻ በአስቸኳይ መቆም አለበት!



የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)
Ethiopian People’s Revolutionary Party (EPRP) (ዴሞክራሲያዊ/Democratic)
ዜጎች በሀገራቸው ውስጥ በመረጡት ሥፍራ የመኖር፤ ሠርቶ ሃብት የማፍራት፤ ቤተሰብ የመመሥረት…ወዘተ በማንም ሊሰጣቸው ወይም ሊነፈጋቸው የማይችል ሁለንተናዊ የዜግነትEthiopian People's Revolutionary Party (EPRP Democratic)መብቶቻቸው ናቸው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በዓለማችን የተነሱ የጎሣ እንቅስቃሴዎች ሁለንተናዊ የዜጎችን መብቶች በሚፃረር መልኩ አንድ-ወጥ የሆነ ወይም ከሌሎች ዘር የፀዳ ሀገርና መንግሥት ለመፍጠር ጥረዋል። ዓላማቸውን ሊያሳኩ ባልተቻሉባቸው ኅብረብሄር በሆኑ አገሮች ውስጥ ደግሞ የኤኮኖሚ፤ የፓለቲካና የወታደራዊ ኃይሉን በአንድ ዘር የበላይነት ለመያዝ ሲባል የዘር ማጽዳት ዘመቻ (ኤትንክ ክለዚንግ)ና የዘር ማጥፋት ዘመቻ (ጄኖሳይድ) ወንጀል መፈጸም የተለመደ ክስተት ሆኗል።
በዘጠናዎቹ መጀመሪያ ላይ የምሥራቁ የሶሻሊስት ካብ በተፈረካከሰበትና የሥልጣን ክፍተት በተፈጠረበት ወቅት፤ እነዚህ የጎሣ የወንጀል ቡድኖች በሕዝብ ውስጥ የነበሩ የፍትህ፤ የእኩልነትና የነፃነት ትክክለኛ ጥያቄዎችን በማጣመምና ለራስ እኩይ ዓላማ በማዋልና ሕዝብን በማሳሳት የጎሣ ወታደራዊ ኃይሎችን በማቋቋም አሰቃቂ የዘር ማጽዳትና የዘር ማጥፋት ወንጀሎችን ፈጽመዋል። ዓለምአቀፍ የዜና ሽፋን ባገኙት ሀገሮች፤ ለምሳሌ በዩጎዝላቪያ፤ በሩዋንዳ፤ በኮንጎ፤ በሱዳን….ወዘተ ወንጀለኞቹ በዓለምአቀፍ ፍርድ ቤት መፈለጋቸውና አንዳንዶቹም ተይዘው ለፍርድ በመቅረባቸው ዘግናኝ ወንጀላቸውን እንዲያቆሙ ወይም እንዲሰወሩ አድርጓቸዋል። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች ግን ዓለምአቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ሽፋን ባለማግኘታቸው ወንጀሉ አሁንም በማንአለብኝነት በሰፊ እየተካሄደ ነው።

ትግል… ሽንፈት፤… ድል፤ ሽንፈት…


Temesgen Desalegn Feteh newspaper editorከምሽቱ አንድ ሰአት አልፏል፤ የእጅ ስልኬ ደጋግሞ ቢጮኽም ትኩረት አልሰጠሁትም፡፡ ከጥቂት ሰከንዶች ፋታ በኋላ የቢሮዬ ስልክ ጮኸ፤ አነሳሁት፡፡ ለካስ እንዲህ በአንዱ አልመልስ ስላት፣ በሌላው እያፈራረቀች የምትደውለው ዕድሜዋ ወደ ሰባ እየተጠጋ ያለው አሮጊቷ እናቴ ኖራለች፡-
‹‹አቤት! እናቴ››
‹‹ለምንድነው የዚህን ያህል ስልኩ ሲጮኽ የማትመልሰው?›› ቆጣ ብላ ጠየቀችኝ፡፡
‹‹አስቸኳይ ስራ ላይ ስለነበርኩ ነው››
‹‹ኤዲያ! አንተ ደግሞ ሁል ጊዜ ጠብ ለማይል ነገር፣ ችክ ማለት ትወዳለህ››
…በእርግጥ እናቴ እውነቷን ነው! ችክ ያልኩ ቸካካ ነገር ሳልሆን አልቀርም ፡፡
‹‹ልዕልና›› ጋዜጣ ታግዳለች፤ እንደ‹‹ፍትህ›› እና ‹‹አዲስ ታይምስ›› ሁሉ የስርዓቱ የአፈና ሰለባ ሆናለች፤ የሚገርመው ግን መታገዷ አይደለም፣ የታገደችበት መንገድ እንጂ፡፡ ከዚህ ቀደም ደጋግሜ እንደገለፅኩት አቶ መለስን የተኩት ሰዎች ከእረሱም የባሱ ጭፍን አምባገነኖች ናቸው፡፡ ማንንም አይፈሩም፡፡ እግዚአብሄርንም ቢሆን ‹‹በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ካልተጠመቅህ አምላክ ሆነ እንድትቀጥል አንፈቅድልህም›› ከማለት አይመለሱም፡፡

ወያኔ በአማራ ተወላጆች ላይ የጀመረውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ እንደቀጠለ ነው



ወያኔ ለአማራ ህዝብ፤ ባህልና ታሪክ ያለዉን ጥላቻ ከተራ ጥላቻ አልፎ በተግባር አማራዉን ወደ ማጥቃት ዘመቻ አደገ እንጂ ለአንድም ቀን ቀንሶ አያውቅም። አማራው እንደ ሰው ልጅ የመኖር መብቱ፣GINBOT 7 Movement ስብእናው ተገፎ ከቀየው፣ ከመንደሩ የአፈራውን ንብረትና ገንዘብ እየተቀማ መባረሩ፣ መሰደዱ፣ እንግልቱ ሁሉ የወያኔ የበቀል እርምጃ ነው።
በአሶሳ፤ በደኖና በአርባጉጉ ውስጥ አማራ በመሆናቸዉ ብቻ ህጻናት፤ሴቶችና አረጋዉያን በግፍ ተገድለዋል። ባለፈዉ አመት በደቡብ ክልል ጉራ ፈርዳ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ለረጂም አመታት ከአካባቢዉ ኢትዮጵያዊ ወገናቸው ጋር ተግባብተዉ ይኖሩ የነበሩ የአማራ ብሄረሰብ አማራ በመሆናቸዉ ብቻ ለአመታት ያፈሩትን ንብረት ይዞ የመሄጃ ግዜ እንኳን ሳይሰጣቸዉ አከባቢዉን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለቅቀዉ እንዲወጡ እንዲፈናቀሉ ተደርጓል።
ከመጋቢት ወር መጀመሪያ ጀምሮ ወያኔ በአማራዉ ህዝብ ላይ አዲስና ሰፋ ያለ የጥቃት ዘመቻ ጀምሯል። በደቡቡ የአገራችን ክልል በጉራፈርዳ የጀመረዉን አማራውን ነጥሎ የማጥቃትና የማንገላታት ዘመቻ አሁን ደግሞ በሰሜን ምስራቅ የአገራችን ክፍል በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቀጥሏል።

የችግራችን ጥልቀቱ – መክፈቻው መጥፋቱ



ዘግይቼ ነበር ይህን ጹሑፍ ከከረነት ያዬሁት „የሲፒጄውን ተሸላሚ” ዳዊት ከበደን መጨረሻ ማየት ናፈቀኝ ከጸሐፊ ክፈሌ ስንሻው አኔሳ“
እኔ ብዙም ድህረ ገፆችን አልጎበኝም። ውስኖችን ነው የማያቸው። አውራንባ ታይምስን ለመጀመሪያ ጊዜ አሁን ገብቼ አዬሁት። የቀረበውን መረጃና የተሰጠውን አሰተያዬት ማገናዘብ ስለነበረብኝ። ኢሳት መኖሩ፤ መፈጠሩ የሚያንገበግባቸው የመኖራቸውን ያህል የሚያስደስታቸው ወገኖች ደግሞ እንዳሉ ከተሰጡት አስተያዬቶች ማንበብ ችያለሁ። ሁሉም የራሱን፤ የሚመስለውን፤ የግሉን አስተያዬት መስጠቱ መብት ነው። ነፃነት ፈላጊነታችን የሚለካበት፤ የሚሰፈርበት፤ የሚመዘንበት መሰፈርቱ ይህ ነውና። ዕድሉ ቢኖረን ይህን መሰል ነፃነት መስጠት ካልቻልን … ?!
በነፃነት ሕይወት ውስጥ የማይመቸውንም ተቀብሎ ተስማምቶ መኖር። በነፃነት ፍቅር ውስጥ ሁሉም የውስጡን ዘርግፎ እራሱን አስጎብኝቶ፤ ወደ አንድ የሚያስማማ፤ የሚያገናኝ፤ መስመር መጓዝ እንዲችል የፍቅር ሐዲድ መዘርጋት ነው። የሚሰጡ ትችቶች፤ የሚጠቀሱ ድክመቶች፤ የሚጠረቡ አስተያዬቶችን ተከታትሎ በአዎንታዊ ዕይታ ሊስተካከሉ የሚገባቸውን በማስተዋልና በመርመር፤ ሊታረቁ የሚገባቸውን በትእግስት በማስታረቅ፤ የተዛቡትን በአዎንታዊ ቅን ዕይታ በማረቅና በማስተካክል ወደሚፈለገው አቅጣጫ ማቅናት የሚፈለግ ሲሆን፤ ይህንንም ወደነውና ከልብ ተቀብለነው ልናሳተናግደው የሚገባ ክስተት ሊሆን ይገባል። ከሁሉ በላይ ልምድና ተመክሯችን ከግብታዊነት ሊያድን እንዲችል በፍጹም ልቦናችን ልንፈቅድለት ይገባል።

Eskinder is a hero to the world but a villain to Meles Zenawi and his disciples



Right in Prison, Wrong on the Throne


Last April, I wrote a “Special Tribute to My Personal Hero Eskinder Nega”.  In that tribute, I groped for words as I tried to describe this common Ethiopian man of uncommon valor, an ordinary journalist of extraordinary integrity and audacity.
Standing with Ethiopia's tenacious blogger, Eskinder Nega - CPJ blog
Eskinder Nega
Frankly, what could be said of a simple man of humility possessed of indomitable dignity? Eskinder Nega is a man who stood up to brutality with his gentle humanity. What could I really say of a gentleman of the utmost civility, nobility and authenticity who was jailed 8 times for loving liberty?  What could I say of a man and his wife who defiantly defended press freedom in Ethiopia, even when they were both locked up in Meles Zenawi Prison just outside of the capital in Kality for 17 months! What could anybody say of a man, a woman and their child who sacrificed their liberties, their peace of mind, their futures and earthly possessions so that their countrymen, women and children could be free!?
Ethiopian journalist Eskinder Nega is a special kind of hero who fights with nothing more than ideas and the truth. He slays falsehoods with the sword of truth. He chases bad ideas with good ones. Armed only with a pen, Eskinder fights despair with hope; fear with courage; anger with reason; arrogance with humility; ignorance with knowledge; intolerance with forbearance; oppression with perseverance; doubt with trust and cruelty with compassion. Above all, Eskinder speaks truth to power and to those who abuse, misuse, overuse and are corrupted by power.