Monday, February 11, 2013

አቶ ስብሓት ነጋ ፍርዳቸውን ሲጨርሱ…



ሐራ ዘተዋሕዶ
  • ‹‹ዕርቅ ለመፈጸም በማለት ሰዎችን ሲልኩ የነበሩ ቄሶች መሰቀል አለባቸው፡፡››
  • ‹‹ታምራት ቤተ ክርስቲያኒቱን ይቅርታ ሊጠይቅ አይችልም፡፡››
  • ‹‹[ሲኖዶስ ማቋቋም] በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከግራኝ ከጉዲት የባሰ ትልቅ  ወንጀል ነው፡፡››
  • <‹ኣቦይ ስብሃት አረጋዊ ናቸው፤ ይሄ የመነጣጠል አባዜ ቢቀርባቸውና ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደው የተጣላ ቢያስታርቁይሻላቸዋል፡፡. . .አርባ ዓመት ሙሉ ቀውስ አታቀጣጥሉ በሉልኝ፡፡›› /አቶ ኣስገደ ገብረ ስላስ ለኢትዮ ምኅዳርጋዜጣ/
ላይፍ፡- አንድ ጉዳይ እናንሣ፡፡ በአሜሪካን አገር የሚገኘው የኦርቶዶክስ ሲኖዶስም ኾነ አራተኛው ፓትርያሪክ ወደ አገር መምጣት የለባቸውም በማለት ደጋግመው ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ ይህ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባት አይኾንም?
Tigray People Liberation Front Split
(አቶ ስብሓት ዛሬ ለንባብ ከበቃው ላይፍ መጽሔት ጋራ ካደረጉት ቃለ ምልልስ)
አቶ ስብሓት፡- የተናገርኹት እንደ አማኝ እና እንደ ዜጋ የግል አመለካከቴን ነው፡፡ መጀመሪያ ፓትርያሪኩን ከኢትዮጵያ የሚያወጣቸው ምክንያት አልነበረም፡፡ ፓትርያሪኩ ኢሕአዴግ ይነካኛል የሚል እምነት አልነበራቸውም፤ ምክንያቱም እንደማንነካቸው ያውቃሉ፡፡ ብንነካቸው እንኳን መሰየፍ ነበረባቸው ወይም ገዳም ገብተው መመነን ነበረባቸው ወይም ኢየሩሳሌም መሄድ ነበረባቸው፡፡
ይህንን ሁሉ ትተው በመጨረሻ ግን ወደ አሜሪካ ወሰዷቸው፡፡ ይህም ሳያንስ በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ ትልቅ ወንጀል በመፈጸም ሲኖዶስ አቋቋሙ፤ የእስልምና አክራሪ እንቅስቃሴን ደገፉ፡፡ እነዚህን ነገሮች ስሰማ ሐሳቤን ገለጽኹ፡፡

አርቲስትና አክትቪስት ታማኝ በየነ በኦስሎ፣ ኖርዌይ (ልዩ አጭር ጥንቅር


የዛሬዋ የእሁድ ምሽት ከታማኝ የኦስሎ የኢሳት ገቢ ማሰባሰብያ መርሃ ግብር ጋር ያሳለፍኩት ምሽት ነበር። ምንም እንኳን መርሃግብሩን በሙሉ ለመፈፀም ባልችልም የአክትቪስት እና አርቲስት ታማኝን በቪድዮ የተደገፈ ገለፃ ግን ለመከታተል እድሉ ገጥሞኛል።
Ethiopian satellite television, norway
ኦስሎ ለኢሳት ገቢ ማሰባሰብያ መርሃግብር ከተገኘው ሕዝብ በከፊል (photo GUDAYACHN BLOG EXCLUSIVE)
ገብስማ ፀጉሩ ከነጭ ሸሚዝ እና ሽሮ መልክ የያዘ ክራቫት ጋር ታማኝን ግርማ ሞገስ አጎናፅፎታል። ታማኝ ወደ መድረኩ ሲመጣ ከታላቅ አክብሮት ጋር ከአምስትመቶ በላይ የሆነው ታዳሚ ከመቀመጫው ተነስቶ ተቀበለው። ታማኝ አፀፋውን እየመለሰ ምስጋናውን ገለፀ። ቀደም ብለው ከጎናቸው ከነበረው ሰው ጋር ይነጋገሩ የነበሩ ሰዎች በፀጥታ ወደመድረኩ ማስተዋል ጀመሩ። ታማኝ ሰላምታውን በአማርኛ ብቻ አልነበረም ያቀረበው ”አሰላም አለኩም” በማለት ለሙስሊም ኢትዮጵያውያን ያለውን አክብሮት ሲገልፅ ሞቅ ያለ ጭብጨባ ተቸረው። ላፕቶፑን አስተካክሎ ከጀርባው በኩል ወዳለው ስክሪን ተመለከተ ትክክል ነው። ንግግሩን ቀጠለ እና እንዲህ አለ-
”ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው በስቶኮልም እና በጄኔቭ ከተመለከትቁት ሕዝብ ኦስሎ ዛሬ የበላይነቱን ይዟል።” ጭብጨባ አጀበው ቀጠለና:-
”…እኔ አርቲስት ነኝ በአርቲስትነት መኖር እችል ነበር። መፅሐፉ የሚለው ከፊትህ ውሃና እሳት ቀርቦልሃል እጅህን ወደወደድከው ጨምር ነው። እኔ እጄን ወደ ውሃ ከትቼ በአርቲስትነቴ እየደነስኩ መኖር አያቅተኝም ነበር። ነገር ግን የእውነት ጉዳይስ? የኢትዮጵያ ጉዳይስ? ዝም ብሎ የሚኖር ህሊና አለን?… እድሜዬ እንደምታዩኝ ላይሆን ይችላል። ፖለቲካ ያቃጥላል፣ ያናድዳል። ሆኖም ግን እስከመጨረሻ ለመፅናት ነው ቃል የገባሁት።”

Friday, February 8, 2013

ፍቅርና አንድነት ያለው ህዝብ ጠላቱን ያሸንፋል



ባለፈው ሂትለርና የወያኔን መሪዎች ባነጻጸርኩበት ጽሁፍ ላይ መለስ ስብሀት በአማራው ህዝብ ላይ በሰፊው ሊያንቀሳቅሱ የሞከሩት እልቂት አንዴት በሚፈልጉት ልክ እንዳልገፋላቸው ሗላ ላይ እናወጋለን ብየ ነበር።
በአለማችን ያሉ ጤናማ መንግስታት በዜጎቻቸው መካከል የመብት ልዩነትና የዘር የቀለም መለያየት፤ ግጭት እንዳይኖር ያለመታከት ይሰራሉ። ይተጋሉ። በኢትዮጵያ ያለው የዲያቢሎሶች መንግስት፤ ሰው በዘሩ ተለይቶ እንዲታወቅ፤ እንዳይስማማም እንዲበላላም ለማድረግ በትጋት ሲሰራ ሀያ ሁለት አመታትን አስቆጠረ።

Charges renewed against Ethiopian journalist Temesghen Desalegn



charges against Ethiopian journalist Temesghen Desalegn
Nairobi, February 8, 2013–The Committee to Protect Journalists condemns the revival of criminal charges against Ethiopian journalist Temesghen Desalegn today in what appears to be a politicized court hearing designed to censor one of the few critical voices left in the country.
A judge in the Federal High Court in the capital, Addis Ababa, revived three charges against Temesghen, former chief editor of the now-defunct Feteh, and one against the general manager of Mastewal Publishing, the publishing company that formerly printed Feteh, according to local journalists who attended the hearing. Temesghen faces charges of “outrages against the constitution,” defaming the government, and false publication of articles, while the manager of Mastewal Publishing faces an unspecified charge for allowing the weekly to be published. Under Ethiopian law, a printing company is also held accountable for a press offense by a publication that it publishes.

Wednesday, February 6, 2013

ተመስገን ስለ አዲስ ታይምስ እንዲህ አለ፤ “የመለስ ራዕይ በ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄት ተተገበረ!!!”


የሁላችንም መተንፈሻ የነበረችው አዲስ ታይምስ የመንግስት ውቃቢ አልወደዳትም እናም ህትመቷ ተቋርጧል። ይህንን አስመልክቶ ተመስገን ደሳለኝ ይህንን ነግሮናል። መርዷችንን እናንብበውማ፤ ቀጥል ተሜ…
ምንም ጥርጥር የለውም መለስ ዜናዊ ፍፁም አምባገነን 

ነበር፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ከአንድ ክፍለ ጦር በላይ የተለየ ሀሳብን እና ነፃ ሚዲያን ይፈራል፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ወራሾቹም ሀሳቡን በነፃነት የሚገልፅን ከመለስ በባሰ መልኩ ይፈራሉ፡፡ ይህ ፍራቻቸው ወደ ጭፍን አምባገነንነት ስለቀየራቸው መላ ሀገሪቷን ወደ ድቅድቅ ጨለማ እየገፏት ነው፡፡
የሆነ ሆኖ መለስ ከአደባባይ ከራቀ በኋላ በፍትህ ቤተሰቦች የሚመራ ትልቅ ሚዲያ ሲዘጋ ‹‹አዲስ ታይምስ›› ሁለተኛዋ ናት፡፡
ለ‹‹አዲስ ታይምስ›› መዘጋት መንግስት የሰጠው ሶስት ምክንያት፡-

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ሳስበው!



«ልጆቼን ከተወለዱ ጀምሮ ለ20 ቀናት ያህል ስለያቸው ይህ የመጀመሪያዬ ነው። ለዚህ ብርታት እና ፅናት እንዲሆነኝ ግን ዘወትር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን አስበዋለሁ። የእስክንድር
Eskinder Nega and his Son Nafkot
እስክንድር ነጋ እና ልጁ ናፍቆት
ልጅ የተወለደው አሁን እርሱ የሚገኝበት እስር ቤት ውስጥ ነው። የሕወሃት ደጋፊዎች ይህንን ሕዝብ ከደርግ ገላገለው እያሉ የሚያደንቁት ስርዓት እርጉዝ ሴት እስር ቤት ውስጥ እንድትወልድ ያደረገ ግፈኛ እንደሆነ ሁሉም ያውቃል። ይህም ሳይበቃቸው ልጁ አምስት ዓመት ሞልቶት እስክንድር ከትምህርት ቤት ሲመልሰው ነበር ድንገት ይዘውት የሚወደው አንድ ልጁ ፊት እጁን ወደኋላ የፊጥኝ አስረው በቪድዮ እየቀረጹ የወሰዱት፣ አሁን የርሱን ልጅና የኔን ልጆች ሳወዳድር የኔ ልጆች በምንም መለኪያ ከ20 ቀናት በኋላ እንደሚያዩኝ እርግጠኞች ናቸው። የእስክንድር ልጅ ግን አይችልም።»
(አርቲስት ታማኝ በየነ አድላይድ/ደቡብ አውስትራሊያ እ.ኤ.አ ጁላይ 2012 )
እውቁ ኢትዮጵያዊ የነፃ ፕሬስ ጀግና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ “አሸባሪ” ተብሎ ለዘጠነኛ ጊዜ የወያኔ እስር ቤት ውስጥ ከተዘጋበት እነሆ ድፍን 16 ወራት ተቆጥረዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥ ብርቅዬው የኢትዮጵያ ልጅ በፈጠራ ወንጀል ያለአግባብ መታሰሩን በመቃወም በአገር ውስጥ የወያኔን የአፈና ድር በጣጥሶ የተደረገ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ባይኖርም፣ በውጭ አገር የሚገኙ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን ግን አልፎ አልፎም ቢሆን ድምፃቸውን በልዩ ልዩ መልክ በማስተጋባት ላይ ይገኛሉ።

Tuesday, February 5, 2013

ትግሉ የሚጠይቀውን መሰዋእትነት ለመክፈል እኛም ዝግጁዎች ነን!

Ginbot 7 weekly editorialቅኝ ገዥዎችን በማሳፈር በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ተጋድሎ ነጻነቷን ጠብቃ የኖረችውና በባርነት ስር ለቆዩ ሀገራት ፋና ወጊ የሆነችው ውድ ሀገራችን ኢትዮጵያ፤ ዛሬ በሀገር ውስጥ ወራሪ በሆነው ህወሃት/ወያኔ መዳፍ እጅ ገብታ በሁሉም ረገድ ከኢኮኖሚ እስከ ሰበአዊ መብት አያያዝ በአለም የመጨረሻዋ የሰው ልጅ መብት ረገጣ የሚፈጸምባት ተስፋ አልባ ሀገር ተብላ ተመድባ ትገኛለች።
ይህችው የቀድሞዋ ኢትዮጵያ በክብርና በኩራት የአፍሪካ የነጻነት ፋናወጊ ተብላ የሚነገርላት፤ በዚህ ዘመን በባርነት አረንቋ እየኖረች፣ ህዝቧ የነጻነት ያለህና የትውልድ የድረሱልኝ ጥሪ ኤሎሄ ለወጣት ልጆቿ  እያቀረበች፣ እየተማጸነች አለች።
ይህን ተከትሎ በሁሉም ግንባር ሀገር በቀል ወራሪ ህወሃት/ወያኔን ታግሎ ለማስወገድ እየተደረገ ያለው ትብብር የሚበረታታ ቢሆንም የወያኔን የከፋፍለህ ግዛ ና የአንድ ዘር የበላይነት ርዕዮተ ዓለምን አስወግዶ ነፃነት ከናፈቀው ህዝብ ጎን በመሰለፍ በሀገራችን የሰላም አየር በሁሉም ከተሞች እንዲሰፍን ለሚደረገው እልህ አስጨራሽ ጉዞ የምናደርገው እገዛ በቂ ነው ብለን አናምንም።