ይህ ፅሁፍ የሚያተኩርበት ዋና ጉዳይ ወያኔ ‚ታላቋን ትግራይ‛ ተብላ የምትጠራ አገር ለመመስረት ሲል በጎንደርና በወሎ ህዝብ ላይ የፈጸመውንና አሁንም እየፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት(genocide) እና ትግራይ ያልሆነ ህዝብን ማፈናቀሌ (ethnic cleansing) ወንጀልች ሊይ ነው። በመላ ኢትዮጵያ የሚደረገውን የኢኮኖሚ ገፈፋና በየትኛውም የመንግስትና የግል የኑሮ ዘርፎች የትግራይ የበላይነት ለማረጋገጥ ሲባል ወያኔ በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ የሚያካሂደውን የሽብር ዘመቻ የዚሁ መሰሪ አላማ አካል ነው። ከዚያ ባሻገር ጎጠኛ አስተዲደር (ethnic federalism) እና የመገንጠል አንቀጽ (አንቀጽ 39) የተባለት አንኳር የወያኔ መርሆች አገልግሎታቸው ወያኔ እንደሚለፍፈው የብሔሮችን እኩልነት ለማረጋገጥ ሳይሆን ሌሎች ብሔሮችን በማፈናቀልና በማራቆት የትግራይ ክልልና የትግራይ ተወላጆች ሀብት እንዱያካብቱና ለሚመሰርቷት ታላቋ ትግራይም ስትራቴጂካዊና ውሀ ገብ ለም መሬቶችን ለመንጠቅ እንዲያመቸው ያስቀመጣቸው ለመሆናቸው ይህ ጽሁፍ አባሪ መረጃዎች ያቀርባል። ወያኔ በጎንደርና በወሎ ህዝብ ላይ የሚፈጽማቸው ወንጀሎች በግብታዊነት የተከሰቱ ሳይሆን ለረጅም ጊዜ በተጠና እቅድ መሰረት ነው።

ወንጀሎቹ ከሞላ ጎደል የሚከተለው ቅደም ተከተል አላቸው።
1. ለምና ስትራቴጂካዊ (strategic) የሆኑ ቦታዎችን ትግራይ ካልሆኑ ህዝቦች በመንጠቅ በትግራይ ክልል ስር እንዲጠቃለሉ ማድረግ፤
2. በተነጠቁ ቦታዎች ላይ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የትግራይ ሰዎችን ማስፈር፤ ከትግራይ ክልልና ከማእከላዊ የወያኔ መንግስት በሚለገስ ገንዘብ አማካኝነት አዲስ የትግራይ ሰፋሪዎችን ሀ) ማስታጠቅ፣ ለ) በእርሻና በሌላ የልማት መስኮች ማደርጀት፤
3. በአዱስ ታጣቂ ሰፋሪዎች አማካኝነትም በነባሩ ህዝብ ሊይ የማፈናቀልና የማሳደድ ዘመቻ በመክፈት አካባቢውን የትግራዮች ብቸኛ ሀብት ማድረግ፤
4. መስፋፋቱንና በሃይል መፈናቀሉን በቆራጥነት የሚቃወሙትንና በነዋሪው ህዝብ ዘንድ ተሰሚነት አላቸው የሚሏቸውን ግለሰቦችን ማፈን፣ ማሰርና መግደል፤ የቀሩትን ሰዎች በማንገላታት ቢቻል ክልሉን ለቀው እንዲሰደዱ ማዴረግ ካልተቻለ ደግሞ ለምነት በሌላባቸው መሬቶች ተጨናንቀውና ተጣበው እንዲታሰሩ በማዴረግ ለከፍተኛ ችግርና ረሀብ እንዱጋለጡ ማድረግ፤
5. የኗሪውን ህዝብ የደረሱ ልጃገረዶች በትግራይ ጎረምሳ ኮርማዎች ማስደፈር፤ (rape ማስደረግ)፤ በዚህ ባህልን፣ ሃይማኖትንና ሰብአዊነትን ባዋረደ ተግባር የትግራይ ዘር ያላቸውን
ልጆች እንዲወልዱ ማድረግና ከዚያ በበለጠ ደግሞ ሌላ ትግራይ ያልሆኑ ወላጆችንና ወንድ ወጣቶችን ቅስም መስበር ነው።