Thursday, February 28, 2013

የፍርሃትና ስም ማጥፋት ፖለቲካ በኢትዮጵያ

2011፡ የሙስና አገዛዝ፤ ፍርሃትና ሰም ማጥፋት

Ethiopia The Politics of Fear in the police statesበዲሴምበር 2011 ‹‹ኢትዮጵያ የደም ሃገር ወይም የንቅዘት (ሙስና) ሃገር›› በሚል ርእስ የኢትዮጵያን ሁለት ገጽታ በማመዛዘን አንድ ጦማር አስነብቤ ነበር፡፡ በዚያን ወቅት ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል በተባለው ተቋም ተቀምጦ የነበረው ገጽታ ያሳየው ኢትዮጵያ ለም መሬቶች በተንኮል በተጠቀለለ ስውር ደባ እየተቸበቸቡ እንደነበር ነው፡፡በዘገባው ላይ ተቋሙ ለኢትዮጵያ ያሰፈረው ነጥብ (10 ከሙስና የፀዳ ማለት ሲሆን 0 ደግም በሙስና ንቅዘት ያጨማለቀው ማለት ነው) ኢትዮጵያ 2.7 ነበር ያገኘቸው፡፡ በሙሰና ከታወቁት የኣለም ሃገሮች ዋነኛዋ ኢትዮጵያ ናት ይል ነበር::  የግሎባል ፊናንሻል አንተግሪት ድርጅት ደግሞ ባለፉት ፲ ኣመታት ከኢትዮጵያ 11.7 ብልዖን  ያሜርካን ብር በሀገወጥ መንገድ ከኣገሪቷ ወጥቶአል ብሎ ዘገቦ ነበር::
ባልፈው ኣመት: አሁንም በስላጣን ላይ ያለው ገዢ ኣስተዳደር ኢትዮጵያን በሽብርተኞች ማነቆ ውስጥ ተወጥራ እንዳለች ሃገር አድርጎ ለማቅረብ ባወጣው የልመናና የገንዘብ መቧገቻ እቅዱ ባለሶስት ክፍል የፕሮፓጋንዳ የቅጥፈት ታሪክ ‹‹አኬልዳማ›› በማለት (ወይም የደም መሬት በማለት ከአክትስ 1፡19 በመዋስ፤ የአስቆሮቱ ይሁዳ ክርስቶስን ክዶ በመሸጥ ባገኘው ገንዘብ የተገዛ መሬት) ከልብ ወለድ የማይሪቅ ትርኢት ለሕዝብ ኣቅርቦ ነበር፡፡ ይህም ትርኢት በአትዮጵያና በኢትዮጵያ ዲያስፖራ ሰዎች በሚታገዝና በሃገርም ውስጥ ባሉት የሚደገፍ የሽብር ተግባር አምባ አድርጎ ለማሳመን የተሰራ ነው፡፡ አኬልዳማ ሲጀምር በኢትዮጵያ ውስጥ ሊከሰት የሚችል በማለት የደም ጎርፍ መምጣት እንደሚችልና፤ ሸብር ዓለምን በማጥፋት ላይ ነው፡፡ ‹‹አኬልዳማ›› ሲተረት: “ሽብርተኝነት የቆምንበትን መሬት እያነቃነቀ፤ ዕለታዊ እንቅስቃሴያችንንም እየገታ መሆኑን በቅጥፈታዊ ፈጠራ ለማሳየት የቀረበ ትርኢት፡፡ አሁን እየተናገርኩ ያለሁት ስለዓለም አቀፉ ሥብርተኝነት አይደለም፡፡ እኔ እያልኩ ያለሁት በገዢው መንግስት ለኢትዮጵያ የተቀመጠውን የቅጥፈት ፕሮፓጋንዳና በዚያም ውስጥ ስለተካተተው አኬልዳማ ተብሎ ስለተቀፈቀፈው፤ ሸብርተኝነት ለኢትዮጵያ አስጊና አሳሳቢ ችግር ነው…… ስለተባለው ነው፡፡”

የሕወሐት ፍጥጫ ቀጥሏል

 “አሁን ያለው ሕወሐት ቆዳ ነው” እነ ስብሃት
“የሕወሐት ወራሾች እኛ ነን” እነ አባይና አዜብ

ሁለት ቦታ የተከፈለው የሕወሐት አመራር ልዩነቱን በማስፋት እየተወዛገበ መሆኑን ከመቀሌ ታማኝ ምንጮች ገለፁ። ስብሃት እና አዜብ የሚመሩት ሁለቱ ቡድን አነጋጋሪ አቋም ይዞ መውጣቱን ምንጮቹ ጠቁመዋል። በስብሃት ነጋ የሚመራው ቡድን ባስቀመጠው አቋም « መለስ ሕወሐትን ገድሎ ነው የሔደው! አሁን ያለው ሕወሐት ቆዳ ነው። ጥያቄው ግልፅ ነው፤ ሕወሐት መቀጠል አለበት.. ወይስ የለበትም?» ሲሉ በድርጅቱ ቀጣይ ሕልውና ላይ ጥያቄ አሳርፈዋል። ከዚህ በተቃራኒ የቆመውና አባይ ወልዱ፣ አዜብና ከጀርባ በረከት ስምኦን ያሉበት ቡድን በበኩሉ « የሕወሐት ወራሾች እኛ ነን፤» ሲል ለነስብሃት ምላሽ መስጠቱ ታውቋል። በተጨማሪ በሁለቱም ቡድኖች በልዩነት ነጥብ ተደርጎ የተወሰደው በ1993ዓ.ም ከፓርቲው የተባረሩት አመራሮች « ይመለሱ» ፣ « አይመለሱም» የሚለው እንደሚገኝበት ተጠቁሟል። የሁለቱም ጐራ ፖለቲካዊ ግብ አንዱ ሌላኛውን ገፍትሮ ከሜዳው ማስወጣትና ፓርቲውን ብሎም አገሪቱን በፈላጭ ቆራጭነት ለመቆጣጠር ያለመ እንደሆነ አንድ የፓርቲው ቅርብ ሰው ጠቁመዋል።

Wednesday, February 27, 2013

ከዘመኑ ጋር መዘመን ያቃተው ህውሃት



የዘረኛው የህውሃት ስርዓት በነፃ አውጪ ስም ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ እንዲሁም ከዛም በፊት የሚከተለው የተሳሳተ ሃገር መገነጣጠሉንና ቤሄራዊ ጥቅምን አሳልፎ መስጠቱንtplf rotten apple መመልከት የተለመደና የቀን ከሌት ክንውናቸው መሆኑ በሃይል ስልጣን ከያዙበት ጊዜ ጀምሮ የሚታይ እውነታ ነው፡፡
ከምስረታው ጀምሮ ይዞት የተነሳው የኢትዮጲያን ሉዋላዊነት የማፍረስና የመበተን አላማውን መተግበር የጀመረው የሻቢያ አሽከር በመሆን ለሃገር አንድነትና ክብር ዘብ የቆመውን የኢትዮጲያ መከላከያ ሰራዊት በመውጋት ሃገራችን ያለ ባህር በር እንድትቀርና በኢትዮጲያዊነት የታነፀውን ዘመናዊ የወታደር ሃይል በትኖ በምትኩ የአንድ ብሄር የበላይነት የሚታይበት፣ ቤሄራዊ ስሜት የሌለው፣ በአለቆቹ ከመታዘዝ ውጪ የወታደራዊ ሳይንስ እውቀት ያልዘለቀው ጀሌዎቻቸውን በህዝብ ላይ አንግሰው ያሻቸውን ሲገሉ፣ የሻቸውን ሲያስሩ እንሆ አሁን ያለንበት ደርሰናል፡፡
በመሰረቱ ይህ እኩይ ስርዓት(ቡድን) በኢትዮጲያዊነት ላይ ካለው የመረረ ጥላቻ የተነሳ አብረው የመሰረቱትን ግን በኢትዮጲያዊነት ላይ ፅኑ አቋም የነበራቸውን ባልንጀሮቻቸውን ሳይቀር እያስወገዱና እያባረሩ በምግባር የሚመቻቸውን በተለይ በህዝብና በሃገር ላይ የጠለቀ ጥላቻ ያላቸውን አስከትለው የጥፋት ዘመናቸውን ቀጥለውበታል፡፡
በተለይ የመንግስት ስልጣን ከያዙ በሗላ ከስልጣን በተጨማሪ በገቢ እራሳቸውን ለማጠናከር ከኢትዮጲያ ህዝብ በዘረፉት ሃብትና ንብረት በትግራይ ህዝብ ስም ባቋቋሙት ኢፈርት ሃገሪቱን ጫፍ እስከ ጫፍ በመቆጣጠር የንግዱን መስክ በበላይነት በመያዝ ገቢና ወጪው የማይታወቅ ትልቅ የሃብት ምንጭ በመፍጠር የአገሪቱን የትኛውም የንግድ እንቅስቃሴ በበላይነት ይዘው ነግሰውበታል፡፡

የመናገር ነጻነት ዘመቻው ለህወሃት መራሹ መንግስት ምኑ ነው?


From Borkena blog/ ቦርከና
ሰሞኑን የዞን 9 አባላት የብሎጋቸውን በኢትዮጵያ መከልከል ተከትሎ ከክፈቱልን ያለፈ ፤ መሰረታዊ ሊባል የሚችል ዘመቻ በማህበራዊ ድህረ ገጾች ጀምረዋል፡፡ በዚህ ደረጃ ምላሽ መስጠቱ እና መጠቀም የሚቻለውን መድረክ ተጠቅሞ የችግሩን ጥልቀት ለማመላከት መሞከር ጥሩ ነው። ነገር ግን የመጻፍ እና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እየተጠየቁ ያሉትን ቡድኖች(‘ፎርማሊ’ ካወራን መንግስት ናቸው -ያውም ፈላጭ ቆራጪ) ባህሪ  ግምት ውስጥ በማስገባት፤ ዘመቻው እነዚሁ ቡድኖች አምነትውበት በማናለብኝነት የወሰዱትን ርምጃ ከማስቀየር ይልቅ በስነ ልቦናቸው ለተቀረጸው የትምክህት እና የበላይነት አስተሳሰብ ሃሴት የሚሰጥ ሆኖ ስለተሰማኝ ለነሱ ትምክህት ሃሴት ላለማዋጣት ስል በዚህ በዘመቻ አልተሳተፉኩም።
እንኳንስ የመናገር ነጻነት አይደለም ለእምነት ነጻነት ጀርባቸውን ሰጥተው የክስርቲያኑን የእምነት ተቋማት በቁጥጥር ስር አድርገው ሙስሊሙንም እንዲሁ እምነቱን ለመንጠቅ ቤት ለቤት ጭምር አሰሳ የገቡ ሰዎች ናቸው፡፡ የመናገር እና ሃሳብን የመግለጽ ነጻነት ጋር በእጂጉ የተቆራኘ  የጋዜጣ ህትመት ማስቆም ሳያንሳቸው ዜጎችን –ያውም ኩሩ ሀገር ወዳድ ዜጎችን በሽብረተኛነት በመክሰስ ፣ብዙ እንግልት በማድረስ እና ክብራቸውን ጭምር ለማዋረድ በመሞከር ሌሌች ዜጎች የዜግነት ክብር እና ነጻነት  ጥያቄ ቅብጠት እና በህይወት መቀለድ እንዲመስላቸው በማድረግ የባርነትን እስተሳሰብ በደህንነት ተቋማት ፣በህግ ተቋማት እንዲሁም የማህበራዊ ድንዝዝነት በሚያስፋፉ ሌሎች ልማዶች የሚስፋፉበትን መንገድ በስውርም በግልጽም በማበረታታት  የባርነትን መስረት ለማጽናት ሌት ከቀን የሚሰሩ ለመሆናቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁኔታ ያለ ብዙ ምርምር ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።

ወያኔ ቅዠት እንጂ ራዕይ የለውም!



ትላንት የተናገሩትን ዛሬ፤ ዛሬ የተናገሩትን ነገ የማይደግሙ ከሀዲ አንባገነን እና ዘረኛ ቡድኖች የስልጣን ኮረቻ በሀይል ከተፈናጠቱበት እለት ጀምሮ የተለያዩ የማወናበጃ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ የበርካታ ንጹሀን ዜጎችን ህይወት ቀጥፈዋል አስቀጥፈዋል፡፡እንኳን እንደጠላት የሚቆጥሩትንና በመርሃ ግብራቸው ነድፈው መጥፋት አለበት ብለው የፈረጁትን ህዝብ ቀርቶ አርነት እናወጣሀለን እያሉ ክእናንተ በመፈጠራችን ኮራንባችሁ የሚሏቸውን የትግራይን ንጹሀን ዜጎች ሳይቀር  የራሳቸውን የስልጣን ዕድሜ ለማራዘም ውድ ህይወታቸውን እንዲገብሩ አድርገዋል፡፡ የሀውዚንን ጭፍጨፋ አቀናብረዋል፣በ1991ዓ.ም በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል በተደረገው  ጦርነት ከ70000 በላይ የጠርነቱ ሰለባ ሁነዋል፡፡አልሻባብን ለመደምስስ በሚል በሶማሊያ በረሃ የረገፉትን ወታደሮች ቤት ይቁጠራቸው፡፡ስልጣን ለወያኔ ከምንም ነገር በላይ ነው፡፡ ስልጣን ከሉአላዊነት፣ከባህር በር ፣ከሀገርና ከህዝብ እንደሚበልጥባቸው ከመጀመሪያው ጀምሮ የወሰዷቸው እርምጃዎች ማሳያ ናቸው፡፡የገንዛ ሀገሩን ቆርሶ ለሱዳን የሚሰጥ፣የባህርበር አያስፈልገኝም የአሰብን ወደብ ውሰዱት፣ኤርትራ እንድትገነጠል ፈቅጃለሁና እውቅና ስጡልኝ እባካችሁ እያለ የአለም መንግትታትን  የተማጸነ፣የገንዛ ዞጎቹን አፈናቅሎ ለውጭ ባለ ሀብቶች መሬታቸውን የሚሰጥ፤የሀገሪቱን ሀብት ለተደራጁ ወንበዴወች የሚያስዘርፍና የሚዘርፍ፤ሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦችን አጥፍቼ  ታላቋን ትግራይን እመሰርታለሁ ብሎ የሚንቀሳቀስ አንባገነን እንዴት ያለ ሀገራዊ ራዕይ ነው የሚኖረው፡፡
ዘረኛው መንግስት በተለያዩ ጊዜያት እንዱን ብሄር በሌላው ብሄር ላይ በማነሳሳት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩት ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው ሀብትና ንብረታቸውን ተዘርፈው ለከፍተኛ ችግር ሲዳረጉ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ለእልፈት ተዳርገዋል፡፡የፖለቲካ ፓርቲዎችና ጋዜጠኞችን  በሽብር ስም እያሰረ ንጹሀንን ሲያሸብር ቆይቷል፡፡በርካታ ፓርቲዎች በሰርጎ ገብ ሰላዮች የተነሳ ይዘውት የተነሱትን አላማ እና  የህዝብ አደራ እዳር ሳያደርሱ በጅምር ቀርተዋል፡፡በወያኔ መሰሪ ተንኮል በተቀነባበረ ሴራ ጦርነት ውስጥ ያልገባ ክልልና ብሄር ባይገኝም ውጤቱ እንደሚፈልጉት ስላልሆነላቸው እና የኢትዮጵያ ህዝቦችም ባላቸው አርቆ አስተዋይነትና ረጅም ጊዜ በሰላም አብሮ የመኖር ባህሉ በመታገዝ  የፕሮፖጋንዳቸው ሰለባ ባለመሆናቸው ለወያኔዎች ትልቅ ራስ ምታት ጥሮባቸዋል፡፡እስካሁን ሲጫወትበት የነበረውን ካርድም እንዲቀይርም ተገዷል፡፡ አዲሱ የመጫወቻ ካርድም ከብሄር ግጭት ወደ ሐይማኖታዊ ግጭት ለማሸጋገርም የሚያስችለውን “ጀሀዳዊ ሀረካት”የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም በመስራት ከ1500 አመት በላይ አብረው የኖሩትን ሁለቱን ታላላቅ እምነቶች ማለቂያ ወደሌለው ጦረነት በመማገድ የስልጣን ጊዜውን ለማራዘም ቢምክርም እናንተ ከመጣችሁት ገና 21 ዓመታችሁ ነው እኛ ደግም ለረጅም ጊዜ  በፍቅር አብረን ኑረናል፤  የጋራ ጠላታችን ዘረኛው ወያኔ ነው፡፡እኛ ከእነሱ እንሻላለን አንለያይም እያሉ በየአደባባዮ አንገት ላንገት ተቃቅፈው እየተላቀሱ ቁጭታቸውን ሲገልጹ መመልከት የተለመደ ተግባር ነው፡፡ሰሞኑን ለኢሳት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕርግራም ሙኒክ ላይ የታየውም ህብረት የዚሁ አካል ነው፡፡
እንዴት እንደ  ኢትዮጵያ ያለች ታላቅ ሀገር እና እንደ ኢትዮጵያውያን ያሉ ቀደምት ህዝቦች እንደ ወያኔ ባሉ ትንሽ ሰዎች ይገዛሉ?እንዴት የአለም ማህበረሰብ በሀሰት የወያኔ ፕሮፖጋንዳ ሲታለል ይኖራል?እስከመቼ ብቻቸውን በምርጫ ተወዳድረው አሸነፍን እያሉ ሲያላግጡ ይኖራሉ? ወያኔዎችስ በቀጣይ ምን የማደናገሪያ ስልት ያመጡ ይሆን? እኔ በበኩሌ በቃ ብያለሁ፡፡ ወያኔ ራዕይ የለውም ኑሮትም አያውቅም፤ ወደፊትም አይኖረውም፡፡የወያኔ  ሀገር እና ህዝብ የማውደም ቅዠት እንጂ ሀገራዊ ራዕይ ብሎ ነገር አያውቅም፡፡በጋራ ጠላታችን ላይ በጋራ እንነሳ!!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Monday, February 25, 2013

ያላስተዋልነው የአቶ ሽመልስ ከማል ቃለ መጠይቅ (ክፍል ሁለት)



ድምፃችን ይሰማ
አቶ ሽመልስ ኡስታዝ አቡበከርን ‹‹አጥፍቶ ጠፊ›› ብለው መዝለፋቸውን ሰምተዋል?
‹‹መንግስት መፅሐፍ ቅዱስንና ቁርአንን ጠቅሶ ክርክር ውስጥ ሊገባ አይችልም፡፡››
የአመቱ ምርጥ ቀልድ
አቶ ሽመልስ ኢቲቪ ከዶኩመንታሪው በኋላ በስህተት ባስተላለፈው የቪዲዮ ፊልም ውስጥ የኮሚቴያችን ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበክር አህመድ በካቴና ተጠፍሮ መታየቱን አስመልክተው በሰጡት ምላሽ ደግሞ ክፋት የተመላበት ንግግር ተናግረዋል፡፡ ‹‹ራሴን አጥፍቼ እጠፋለሁ፣ ወደ ጥፋትና ወደ ሽብር ሥራ እገባለው ያለ ሰው ለጥንቃቄ ተግባር ሲባል በካቴና እጁን እንዲታሰር ማድረግ የየትኛውንም ህግ የሚጥስ አይደለም›› ብለዋል፡፡ ይሄ ወንጀል ነው! አንድን ነጽህና የሚልዮኖች ውክልና ያለው ዜጋ ‹‹አጥፍቶ ጠፊ›› ሲሉ መሳደብ ለአንድ ባለስልጣን አሳፋሪ ነው፡፡ ኡስታዛችን አንድም ቀን እንኳን እንዲህ ያለ ንግግር ተናግሮ አያውቅም፡፡ እጅግ ሰላማዊና ሰላምን ሲሰብክ የቆየ ሰው ነው፡፡ ሁልጊዜም ሚዛናዊ አስተሳሰብ ያለው አስተዋይ መሪያችን ነው፡፡ መንግስት መሪዎቻችንን ለማሰር ባሰበበት ወቅት እንኳ እኛ ብንታሰር ከስሜታዊነት ራቁ! ሲል ነው ህዝበ ሙስሊሙን ቃል ያስገባው፡፡ ይህን ለሚሊዮኖች ተምሳሌት የሆነ ሰው ‹‹አጥፍቶ ጠፊ›› ሲሉ መሳደብ ወንጀል ነው – ምን ያደርጋል! ይህን እንኳ የሚያርም የአስተዳደርም ሆነ የፍትህ ስርአት የለም እንጂ፡፡ያላስተዋልነው የአቶ ሽመልስ ከማል ቃለ መጠይቅ (ክፍል ሁለት)
አቶ ሽመልስ በቃለ መጠይቃቸው ሌላ ቦታ ላይ የተናገሩት ንግግር ደግሞ መንግስት እስልምናን ለማጥፋት ቆርጦ የተነሳ መሆኑን የሚያረጋግጥ ይመስላል፡፡ ‹‹በየሲዲው ፀብ ቆስቋሽ ፕሮፓጋንዳዎችን የሚያስፈፅሙት፣ በቲቪ አፍሪካ የተለያዩ ቻናሎችን በመጠቀም የሚያሰራጩት እነዚሁ አክራሪዎችና ሽብርተኞች ናቸው›› ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በንግግራቸው ውስጥ እንደምናየው ሁሉንም ነገር በባዶ ከመወንጀል ያለፈ ያቀረቡት ማስረጃም የላቸውም፡፡ ሰላማዊ የእስልምና ትምህርት እየሰጠ የሚገኘው ቲቪ አፍሪካ ለምን ኢላማቸው ሆነ? ህገ መንግስታችን የሃይማኖቶችን ሰበካ የማድረግ መብት አስጠብቆ የለም እንዴ? ይህን መብት በመጠቀም ሁሉም ሀይማኖት ሰበካ እያደረገ አማኞቹን ያስተምራል፡፡ ቲቪ አፍሪካም ያደረገው ይህንኑ ሆኖ ሳለ ጸብ ቀስቃሽ እየተባለ ነው፡፡ ጣቢያው ምንድነው ጥፋቱ? ኢትዮጵያ ምድር ላይ እስልምናን መስበክ ክልክል የሚያደርግ አዲስ ህገ መንግስት ሳናውቀው ወጥቶ ይሆን?
ከአቶ ሽመልስ ከማል ቃለ መጠይቅ ውስጥ እስቲ የሚቀጥለውን ንግግር እንመልከት፡፡ ‹‹መንግስት መፅሐፍ ቅዱስንና ቁርአንን ጠቅሶ ክርክር ውስጥ ሊገባ አይችልም፡፡ ይሄ ምድራዊ መንግስት ነው፡፡ የትኛውንም ሃይማኖት አይደግፍም፡፡ የትኛውንም ሃይማኖት የማይቃወም መንግስት ነው፡፡ አለማዊና ምድራዊ መንግስት ነው፡፡››

ያላስተዋልነው የአቶ ሽመልስ ከማል ቃለ መጠይቅ



ድምፃችን ይሰማ
በእርግጥ ግለሰቡ የባለስልጣን ግብር አላቸው?
ባሳለፍነው ሳምንት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ዲኤታ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል ኢትዮ ቻናል ከተባለው ጋዜጣ ጋር አንድ ቃለመጠይቅ አድርገው ነበር፡፡ ጋዜጣው የመንግስት ፕሮፓጋንዳ መንዣ መሳሪያ ከሆኑ ‹‹የግል›› ጋዜጣዎች ውስጥ አንዱ እንደመሆኑ ምን አይነት ይዘት ያለው ነገር እንደሚያወጣ ለብዙዎች ድብቅ አይደለም፡፡ ያወጣውም ብዙዎች ከሱ የሚጠብቁትን ፕሮፓጋንዳ አይነት ጽሁፍ ነበር፡፡ ኢቲቪ የፍርድ ቤት ትእዛዝን ጥሶ ባስተላለፈው አሳፋሪ ‹‹ዶኩመንታሪ›› ፊልም የተነሳ የደረሰበትን ውግዘት እና የፕሮፓጋንዳውን መክሸፍ ሊያስተባብሉ ነበር አቶ ሽመልስ ከማል በኢትዮ ቻናሉ ቃለ መጠይቅ ብቅ ያሉት፡፡ያላስተዋልነው የአቶ ሽመልስ ከማል ቃለ መጠይቅ
ቃለ መጠይቁ ከአንድ ትልቅ የመንግስት ባለስልጣን እንደመምጣቱ ጨዋነትን የተላበሰና ደረጃውን የጠበቀ መሆን በተገባው ነበር፡፡ ያ ግን አልሆነም፡፡ አስገራሚ በሚባል ደረጃ ከቃላት አጠቃቀሙ ጀምሮ በሁለመናው ዝቅ ያለ እና የወረደ ነበር፡፡ ቃላቶቹ ተራና ‹‹የመንደር›› ከመሆናቸውም ሌላ ግለሰቡ ኃላፊነት በጎደለው ሁኔታ የሻቸውን የሚናገሩ እንደሆኑ ያሳብቁ ነበር፡፡ አንድ የመንግስት ባለስልጣን የሚናገራቸውን ነገሮች የኋላ ውጤት ያለምንም ማገናዘብ እንዳመጣለት መናገሩ አገራችን ውስጥ በመንግስት እና በግለሰብ መካከል ያለው ለውጥ ከነጭራሹ እየጠፋ መምጣቱን እንድንገነዘብ ያደርገናል፡፡
ግለሰቡ በረዥሙ ቃለ መጠይቃቸው በርካታ ሀሳቦችን አንስተዋል፡፡ ሁሉንም እዚህ እያነሳን ልንነጋገርባቸው ባንችልም የተወሰኑትን ብቻ ጠቀስ ጠቀስ እያደረግን ምልከታችንን እንሰጥባቸዋለን፡፡

የሚሳናቸው የለም

የሚሳናቸው የለም

ውዝግብ በአዲስ አበባው ሲኖዶስ ውስጥ፡ ያሳዝናል! ቤተ ክርስቲያናችን እንዲህ ኹና አታውቅም፤ ይፋረደን!

ውዝግብ በአዲስ አበባው ሲኖዶስ ውስጥ፡ ያሳዝናል! ቤተ ክርስቲያናችን እንዲህ ኹና አታውቅም፤ ይፋረደን!

እያሸበሩ … “አሸባሪ” ፍለጋ … – በነስረዲን ኡስማን

እያሸበሩ … “አሸባሪ” ፍለጋ … – በነስረዲን ኡስማን

Sunday, February 24, 2013

ኢሕአዴግ ምንም መራጭ ባልተመዘገበበት የቦረና ዞን ለምርጫ ሊወዳደር ነው

ኢሕአዴግ ምንም መራጭ ባልተመዘገበበት የቦረና ዞን ለምርጫ ሊወዳደር ነው

ሰበር ዜና፡ አቡነ ሳሙኤል የአቡነ ማቲያስን ለፓትርያርክ እጩነት መቅረብ ተቃወሙ

ሰበር ዜና፡ አቡነ ሳሙኤል የአቡነ ማቲያስን ለፓትርያርክ እጩነት መቅረብ ተቃወሙ

የደም እንጀራ

የደም እንጀራ

አስሩ የጽልመት ቀናት-በኢትዮጵያ !



(ከየካቲት 8/1929 – የካቲት 17/1929 ዓ.ም)

በመስከረም 1927 ዓ.ም የወጣው Detroit Times — (Sept. 22, 1935, p. 3) መጽሔት ከአንድ ታላቅ ሳይቲስትና የፈጠራ ባለሙያ ጋር የኢትዮጵያንና የጣሊያንንEthiopia Against Italian Invasion, picture1 ወረራ አስመልክቶ ቃለ-ምልልስ አድርጎ ነበር፡፡ Nikola Tesla Tells How He’d Defend Ethiopia Against Italian Invasion(www.tesla.hu/tesla/articles/19350922.doc) በቃለ-ምልልሱም ላይ ጋዜጠኛው ዶ/ር ኒኮላ ቴስላን እንዲህ ብሎ ጠየቀው፤ “ካለፈው የካቲት 1935 (እ.አ.አ) ጀምሮ ኢጣሊያን ኢትዮጵያን በኃይል ወራለች፡፡ አንተ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ብትሆን ምን ታደርግ ነበር?” መላሹ ዶ/ር ኒኮላ ቴስላም ትንሽ ጊዜ ትክዝ ካለ በኋላ፤ “እኔ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ብሆን ኖሮ፣ በከተሞች አካባቢ ያለውን ሕዝብ በመላ ወደገጠርና ወደዱር ገደሉ እንዲሄዱ አደርገዋለሁ፡፡ ሕዝቡ ከከተሞች ወጥቶ ወደገጠራማ ቦታዎች እንዲያፈገፍግ አዘዋለሁ፡፡” ጋዜጠኛው ጣልቃ ገባ፤ “ለምን?” አለው፡፡ ቴስላም ቀጠለ፤ “የአሁኗ ኢጣሊያ መሪዎች ክፉኛ ማስተዋል የጎደላቸው ጣሊያኖች ናቸው፡፡ የፋሺዝም ርዕዮት-ዓለም እውር አድርጓቸዋል፡፡ ስለሆነም ከፍተኛ ጭፍጨፋ በከተሞች በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ እንደሚፈጽሙ ይታየኛል፡፡ ስለሆነም ሕዝቡ ከከተሞች ወጥቶ ወደ ገጠራማ አካባቢዎች ወፍለስ አለበት፡፡” ጋዜጠኛው ግራ ገባው፤ ጥያቄዎቹን አዥጎደጎደ፤ “ኢጣሊያ ትልቅ አገርና በሥልጣኔም ቢሆን ከኢትዮጵያ የተሻለች ሆና ሳለ እንዴት እንደዚህ ያለ የአረመኔዎች ግፍ ልትፈጽም ትችላለች ብለህ ታስባለህ?”
ሊቁ ኒኮላ ቴስላ ረጋ ባለ አንደበት መናገሩን ቀጠለ፤ “እንዳልከውና እናንተ ጋዜጠኞቹ እንደምትደሰኩሩት አይደለም፡፡ ኢጣሊያ ከአትዮጵያ የበለጠ ሥልጣኔ የላትም፤ ነገር ግን ቴክኖሎጂውና በዘመናት ውስጥ በጦርነት ምርኮና ዘረፋ ያከማቸችው ሀብት አላት፡፡ ኢትዮጵያ ግን ነፃነቷን ተከላካይ አገር አንጂ ወራሪ ሃይል ሆናም ስለማታውቅ በዝርፊያ የተከማቸ ሀብት የላትም፡፡ በሥልጣኔ በኩል ካየኸው ግን ኢትዮጵያ ጁሊየስ ቄሳር ከመነሳቱና የዛሬዋ ኢጣሊያ ከመፈጠራ በፊት ብዙ ሺህ አመታት በፊት የሰለጠነች አገር ናት፡፡ እናንተ ጋዜጠኞቹና የፋሺስት ፕሮፓጋንዲስቶቹ እንደምታወሩት አይደለም፡፡” ቴስላ ትንሽ ቆም አለ፡፡ ወዲያውም ቀጠል አድርጎ፤ “ይኼንን ስልህ ኢጣሊያ የእነሴኔካ፣ የነጆቫኒ ቦካሺዎ፣ የነፔትራርች፣ የነሊዎናርዶ ዳቬንቺ፣ የነሚካኤል አንጄሎና የነጋሊሊዮ ጋሊሊ አገር መሆኗን እያወቅኩ ነው፡፡ ዛሬ ኢጣሊያ (በ1920ዎቹ ማለቱ ነው) ያ የከያኒነትና የተመራማሪነት መንፈስ ከኢጣሊያ ጠፍቶ፣ በፋሺዝምና በጭፍን ካቶሊካዊነት ልጓም የሚፈረጥጡ ልጆች አገር ሆናለች፡፡” ሲል ለረጅም ደቂቃዎች በትካዜ ነጎደ፡፡

Saturday, February 23, 2013

መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል


በአለፉት ሠላሳ አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ ችግሮችን መፈልፈያ መሣሪያ ሆናለች፤ ለብዙ ምዕተ-ዓመታት ይዘናቸው (ምናልባትም አቅፈናቸው ማለት ይሻል ይሆናል) ስንንከባለል የቆዩ ችግሮች ሞልተውናል፤ እያሰብን እነዚያን የቆዩ ችግሮቻችንን በመፍታት ፋንታ ሌሎች አዳዲስ ችግሮችን እየፈለፈልን የተቆላለፉና የተወሳሰቡ፣ ውላቸው የጠፋ ችግሮችን ፈጥረናል፤ እየፈጠርንም ነው፤ አሁን በመፈጠር ላይ ያለው አዲስ ችግር እስላማዊ መንግሥት በኢትዮጵያ የሚል ነው፤ እስቲ እንመልከተው፡፡መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል
በሩቁ እንጀምር፤ እስላማዊ መንግሥታት ያቋቋሙ አገሮች አሉ፤ አንዳቸውም ሰላም የላቸውም፤ እስላማዊ ቡድኖች በምርጫ አሸንፈው ሥልጣን የያዙ አሉ፤ ለምሳሌ በቅርቡ በአረብ አገሮች በተጀመረው የፖሊቲካ እድገት ለውጥ በቱኒስያና በግብጽ እስላማዊ ቡድኖች አሸንፈው ሥልጣን ይዘዋል፤ በዚህም ምክንያት በቱኒስያና በግብጽ የለውጥ ጥያቄ አገርሽቶ አንደገና ሰዎች እየሞቱ ነው፤ በነዚህና በሌሎችም አገሮች የሚገኙት ወጣቶች የሚፈልጉት የሰው ልጆች ሁሉ መብቶች የሚከበሩባቸውና በሙሉ የግለሰብ ነጻነት የተረጋገጡባቸው አገሮች እንዲኖራቸውና በእኩልነት ኩሩ ዜጎች ሆነው እንዲኖሩ ነው፤ የአንድ አገር ዜጎች የተለያየ ዘር፣ የተለያየ የቆዳ ቀለም፣ የተለያየ ቁመትና ውፍረት፣ የተለያየ ጾታና ዕድሜ፣ የተለያየ ቋንቋ፣ የተለያየ ሃይማኖት፣ የተለያየ የፖሊቲካ አመለካከት፣ የተለያየ ትምህርት፣ የተለያየ ሙያና የተለያየ ገቢ ሊኖራቸው ይችላል፤ የጋራ ማንነታቸው ዜግነት ነው፤ እኩልነታቸው በዜግነታቸው ነው፤ አንድነታቸው በዜግነታቸው ነው፤ እኩልነታቸውንና አንድነታቸውን የሚያረጋግጥላቸውና ሚዛኑን የሚጠብቅላቸው ከበላይ ሆኖ ሁሉንም የሚገዛው ሕግ ነው፡፡

Friday, February 22, 2013

ሰበር ዜና – አስመራጭ ኮሚቴው ለዕጩነት የለያቸው አምስት ሊቃነ ጳጳሳት ታወቁ !!



ሐራ ዘተዋሕዶ
  • ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል እና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል አልተካተቱም
  • ሁሉም የኮሚቴው አባላት በውሳኔው ስለመስማማታቸው አጠራጣሪ ኾኗል
  • የፓትርያሪክነት መመዘኛ መስፈርቱ ከዕጩዎች ማንነት ጋራ በአግባቡ ይረጋገጥ
  • ‹‹ዕጩዎቹን ስታውቅ ፓትርያሪኩን ታውቃቸዋለኽ››› /ሰሞንኛ አባባል/
የስድስተኛው ፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ ለዕጩ ፓትርያሪክነት አጣርቶ የለያቸውን አምስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ለቋሚ ቅ/ሲኖዶሱ ማቅረቡ ተሰማ፡፡ ከየካቲት ዘጠኝ ቀን ጀምሮ የዕጩዎች ልየታ ሲያካሂድ የቆየው አስመራጭ ኮሚቴው÷ ለፓትርያሪክነት ለመመረጥ ብቁ ናቸው ብሎ ያመነባቸው የአምስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ስም ዝርዝር፡-
1)  ብፁዕ አቡነ ማትያስ – በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት ሊቀ ጳጳስ
2)  ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ – የወላይታ ዳውሮ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ
3)  ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ – የባሌ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ
4)  ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል – የከፋ ሸካ ቤንች ማጂ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅ/ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
5)  ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ – የሰሜን ጎንደር ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡
የአስመራጭ ኮሚቴው አጣርቶ ሊያቀርባቸው ከሚችላቸውና የቅድሚያ ግምት ከተሰጣቸው አባቶች አራቱ በኮሚቴው የዕጩዎች ዝርዝር ውስጥ መግባታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡ ኮሚቴው በሚያቀርባቸው ዕጩዎች ውስጥ ያልተጠበቁ አባቶች ሊታዩ እንደሚችሉም አስቀድሞ የተገመተ ነበር፡፡

የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ለአ.አ. አስተዳደር ለመወዳደር መታጨታቸው አነጋጋሪ ሆኗል

የኢሕአዴግ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ለአ.አ. አስተዳደር ለመወዳደር መታጨታቸው አነጋጋሪ ሆኗል

Wednesday, February 20, 2013

የዳውሮ ሕዝብ ያካሄደው መራር ትግልና ውጤቱ፤



Yenesew Gebre from Dawro-Waka Ethiopiaበደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኘው የዳውሮ ዞን ሕዝብ ለሕወሀት መራሹ መንግሥት በተደጋጋሚ ጥያቄ አቅርቦ እንደነበርና ሕዝቡ ላቀረበው ጥያቄ ተመጣጣኝ ምላሽ በመነፈጉ በመንግሥት ላይ በተለያዩ ጊዜያት ማመጹን በተለያዩ የብዙኃን መገናኛዎች ሲዘገብ ሰንብቷል ። የሕዝቡ የልማትና የወረዳ ጥያቄ ከአስር ዓመት በላይ ዕድሜ አለው። ሕዝቡ ከዛሬ ነገ ምላሽ አገኛለሁ ብሎ ሲጠብቅ አልተሳካለትም። በመሆኑም ተስፋ በመቁረጥ ይመስላል ወደ ሰላማዊ ተቃውሞ አመራ።
ሕዝቡ ያቀረበው ጥያቄ የማያሻማና ግልጽ ነበር። የዞኑን ሕብረተሰብ ብዛትና አሰፋፈርን እንዲሁም የወረዳዎችን ጂኦግራፊያዊ አቀማማጥ ከግንዛቤ ውስጥ ባስገባ መልኩ ተጨማሪ ወረዳ ይፈቀድልን ፤ የአንዳንድ ወረዳዎች የወረዳ ማዕከላት ቀደም ሲል የወረዳውን ሕዝብ አማክሎ ከሚገኝበት ቦታ አንስተዉት አብዛኛውን የወረዳውን ነዋሪና ቀበሌያትን ወደ ማያማክል፤ የመጠጥ ውሃ እንኳን ለማግኘት ወደሚቸገርበት ሥፍራ እንዲዛወር ተደረገብን፤ የወረዳው ማዕከል ራቀብን፤ ይህ ብቻም ሳይሆን ምንም የሕዝብ አስተያየት ሳይጠየቅና የብዙኀን ይሁንታ ሳይኖረው በጊዜው የነበሩ የወረዳና የዞን ካድሬዎች እንዳሻቸው በፈቃዳቸው ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ወደ ማያማክለን ሥፍራ አዛውረውብናል በድለውናል። ደጋግመን በየደረጃው ብናመለክት ብናለቅስ ሰሚ አጣን። በዚህ የተነሳ ተቸገርን። ፍትሕ በአግባቡ ማግኘት ተሳነን። ማሕበራዊ ተቋማትንና ልማትን ማግኘት አልቻልንም።  መልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ እንዲኖረን እንሻለን። ወረዳም የልማት አካል መሆኑ ታውቆ መፍትሄ ይሰጠን የሚል ነው።

የታማኝ ጥሪ ለተቃዋሚ ኃይል መሪዎች – ታማኝነት ያፈራውን ህዝባዊ ፍቅር ተረከቡኝ ነው


 

“ህዝቡ መሪዎችን ተጣራ! … ሳትሰሙ ብትቀሩ ግን ግፍ ይሆናል! … እኔ ተራው ሰው ይህንን የህዝብ ጥያቄ የመሸከም አቅሙም ብቃቱም የለኝም! የመነጋገሪያና የመደማመጫ ጊዜያችሁ አሁን ነው! እባካችሁን?!” በማለት የተቃዋሚ ኃይሎችን እንደ ድርጅት የህዝብን ፍላጎት እንዲረከቡና እንዲመሩ ከሰበዕዊ መብት ተሟጋቹ ከአርቲስት ታማኝ በዬነ ጋር በተደረገው ቃለ ምልለስ ከኢሳት Feb 18, 2013 ከዕለታዊ ዜና ጋር አዛምዶ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ካቀረበው የተወሰደ።
“ህዝብ መሪዎችን ተጣራ!” መንገድ ጠራጊው ለአዲስ ምዕራፍ – ብሄራዊ የፍቅር ጥሪ አቀረበ!
Artist Tamagne Beyene on ESAT Newsሥርጉተ ሥላሴ 19.02.2013
ወይ ጉዴ ዛሬ ደግሞ እንዴትና እንዴት አድርጌ ነው ላቀርበው ያሰብኩት ይሆን … እም! ስገርም
የሰብዕዊ መብት ተሟጋቹ አርቲስት ታማኝ በዬነ ከእኛም ሲዊዘርላንድ መጥቶ በነበረበት ጊዜ የተናገረው አንድ ኃይለ ቃል ነበር። „ …ሰው ጠፋና እኔ ሰው ሆኜ ለእኔ እንዲህ ትወድቃላችሁ ትነሳላችሁ …“ እኔ ይህን ሲል … እኔን! አፍር ልብላልህ አልኩኝ። እራሴ ሥርዓቱን በቪዲዮም እዬቀረጽኩት፤ በተጨማሪም በድምጽ መቅረጫም እዬቀዳሁት መሆኔን ዘንግቼ። ትናንትና ሳዳምጠው የእኔንም ድምጽም ቀድቶታል። የቀደሙት ሐዋርያትና ሰማዕታት „እኔ ትቢያ እኔ ታናሽ ስሆን ይሉ ነበር።“ ላቅ ያለ አብነት ነው። እንዲህ ዝቅ ማለት። እራስን ማዋራድ ~ ጸጋ ነው። እራስን ዝቅ ሲያደርጉ ህዝቡ የአንተ ሥፍራ ይህ አይደለም ብሎ፤ ቦታውን አደላድሎ፤ ወዶና ፈቅዶ የመረጠውን ከፍቅሩ ማህደር ያስቀምጣል። ለአርቲስት ታማኝ በዬነ ቦታውን የመደበለት፤ የደለደለለት ህዝቡ እራሱ ነው። በፈቃዱ ወዶና ደስ ብሎት ነው የሰጠው።

በወያኔ ኢትዮጵያ: ቆርጦ ቀጥል ፖለቲካ፣ ቆርጦ ቀጥል ኢኮኖሚ




ሰሞኑን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እየተላለፈ ያለውን አሳፋሪ “ የጀሃዳዊ ሃረካት” ድራማ በአግራሞት ስመለከትና በቅርቡም ይለቀቃል ተብሉ ስለሚጠበቀው “ ነውጥን ናፋቂ የሩቅ አገር ሰዎች” የፕሮፖጋንዳ ቪዲዮ እያሰብኩ ሳለሁ ነው ሌላ ኢኮኖሚያዊ ድራማ በ Addis Fortune ድህረ ገጽ ላይ የተመለከትኩት:: ይህ እኔ ልጽፍ የተነሳሁበት ድራማ በፊት ከጠቀስኳቸው ድራማዎች ለየት የሚያደርገው ፊልሞቹ በሙስሊምና ክርስቲያን ወገኖቻችን ላይ ፍርሃት፣ አለመተማመንና ጥላቻን ለማባባስና የሃማኖት መብት ጥያቄያቸውን ለማፈን በስፋት እየተካሄደ ያለ ዘመቻ ሲሆን  በጽሁፍ መልክ የወጣው ድራማ ግን መንግሥት ላለፉት 7 እና 8 ዓማታት አስመዘገብኩ እያለ በሚላላጥበት የሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የተከሰተውን የቀመር መዛባት ቅሌት ተድበስብሶ እንዲታለፍ እያደረገው ያለ ሴራ መሆኑ ነው::

የካቲት 12 ቀን 2005 ዓ. ም. የሰማዕታት ቀን ሲከበር፣ በጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ተወካይ የተደረገ ንግግር


አርበኞች ማህበር ተወካይ የተደረገ ንግግር

Report on Yekatit 12 Event in Addis Ababa
ክቡራትና ክቡራን
እናት አገራችን ኢትዮጵያ ከብዙ ሺህ ዓመታት ጀምሮ ከቅርብ ጎረቤቶችና ከሩቅ ጎረቤቶች ትንኮሳ ሲካሄድባት በቆራጥ ልጆቹዋ መስዋዕትነት ጠላቶቹዋን ድል እያደረገች እነሆ እስከዛሬ ነጻነቱዋን አስከብራ ኖራለች፡፡

Monday, February 18, 2013

የኢትዮጵያ ትምህርት ፖሊሲና ችግሮቹ



Author Baile Derseh
ባይሌ ደርሰህ ምህረቴ
ወያኔ በ21 ዓመት ቆይታው በትምህርት ፖሊሲው ላይ ይዞት የመጣው የኣንድ ቢሔር ብቻ የመጥቀም ኣላማውን ከግብ ለማድረስ በ1984ዓ ም ኣዲስ የትምህርት ፓሊሲ ቀርፆ 10ዓመት ባልሞላ ውስጥ ሶስት ጊዜ የመማሪያ መጽሐፍትን በመቀያየር ትምህርትን ከግዜ ወደ ግዜ ጥራቱ በማሽቆልቆል ዕነሆ ዛሬ ሞገደኛና በራሱ የማይተማመን ትውልድ ሊፈራ ችሏል። የወያኔን የትምህርት ፖሊሲ በተለያየ ጊዜ ያገባኛል የሚሉ መምህራን፤ተማሪዎችና ወላጆች የትምህርት ፖሊሲዎ ያለበትን ችግርና ያመጣዎን ኣሉታዎ ተግባር በተደገፈ መረጃ ቢያቀርቡም ወያኔ በማንኣለብኝነት ጥያቄዎን ለኣነሱ ሀገር ወዳድ ሙህራን ምላሹ ዕስራት፤ሞትና ስደት ገጥሟቸዋል።
ወያኔ ዕንደፈለገዎ በህዝብ ላይ ዕንዲፈነጭ ሲያደርጉት የነበሩ ምራባዊያን፤ኣሜሪካና ኣለም ባንክ ዛሬ ግን ችግሩ ኣፍጥጦ ወደ ራሳቸው ሲመጣ የችግሩን ኣሳሳቢነት በጥናትና ምርምር በተደገፈ ሰነድ በማስረዳትና ከሌሎች ኣገሮች ጋር በማወዳደር የኢትዮጰያ ትምህርት ፖሊሲ ከፍተኛ ችግር ያለበት መሆኑን በማጉላትና በዚሁ ከቀጠለ ሀገሪቱን ኣደጋ ላይ እንደሚጥላት እየገለጹ በኣስቸኳይ የሁሉም ክፍሎች የትምህርት ካሪኩለም መከለስና መለወጥ እንዳለበት ኣለም ባንክ ኣስጠነቀቀ።

የዋሾ መንግስት ጩኸት፣ ውሸት! ውሸት! ውሸት!




ሰሞኑን ወያኔ የተለመደ የውሸት ድራማ ሰርቶ፤ ሲሞን በረከት በሚባል፤ የማያምር፤ የማያፍር የኤርትራ ሰው፤ ጭራሹን አማራ ነኝ ብሎ እንዲያታልል ወያኔ የቀጠረው ባእድEthiopian Muslims, we are all Abubeker የፕሮፓጋንዳ ሚኒስቴር፤ የሀሰት ፊልም ደራሲና የበላይ አዘጋጅ የሆነ ሰው፤ ሰርቶ ጨርሶ ያሳለፈውን “ጂሀዳዊ ሀረካት” በሚል ርእስ ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት ከሚያደርገው ነገር የተለየ ባይሆንም፤ ቀጣይ የማናደድ ስራቸውን ለኢትዮጵያ ህዝብ አቅርበው ነበር። እንደድሮው አረፍተነገርና የስእል እንቅስቃሴ እየበጣጠሱ፤ ቆርጠው እየቀጣጠሉ፡ እየገጣጠሙ፤ ውሸት እየደራረቱ፤ ለራሳቸው ያሳምናል ብለው እንደመሰላቸው ለኢትዮጵያ ህዝብም ይመስለዋል ብለው በታመመ አእምሮ ስለሚያስቡ ለቀውታል።
ከኢትዮጵያዊው ሙስሊም የመብት ጥያቄ ጋር እንዲሁም ባህሪ ጋር ከቶም ከቶ የማይገናኝ፤ የንጹሀን ሙስሊም ወንድሞቻችንን ስም ለማጥፋት፤ መልካሙን የኢትዮጵያ ሙስሊም ሀይማኖትና ወደር የለሽ መልካም ስነምግባር ጥላሸት ለመቀባት፡ ይህንን ውብ መልኩን ለማጠልሸት፤ ብሎም ከኢትዮጵያዊ ክርስቲያን ወንድሙ ጋር ለማጋጨት ደም ለማቃባት፤(የማይቻል መሆኑን ቢያውቁትም) የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ነዝተዋል።
ኢትዮጵያዊው ሙስሊምና ኢትዮጵያዊው ክርስቲያን ተቃቅፎ፤ ተደጋግፎ፤ በሞት በልደት ተጠያይቆ፤ ተቀባብሮ፤ ተዛዝኖ፤ የሚኖር፤ ክርስቲያኑ የሙስሊሙን አውድአመት አክብሮ፤ ኢድ አልፈጥር፤ ኢድሙባረክ ተባብሎ፤ ሙስሊሙ የክርስቲያኑን አውዳመት አክብሮ እንኳን ለገና እንኳን ለመስቀል አደረሳችሁ ብሎ፡አብሮ በልቶ፤ ጠጥቶ፤ ተደስቶ፤ ሰምና ወርቅ ሆኖ ለዘመናት የኖረ፤ እየኖረ ያለ፤ ወደፊትም የሚኖር ህዝብ ነው።

ወንጀለኛ ሊፈራና ሊሸማቀቅ እንጂ ሊያስፈራራ አይገባውም የውጭውን አለም ከወያኔ ሰላዮችን ማጽዳት ቁጥር 2



ከዚህ በፊት የወያኔ ሰላዮችን ከውጭ አለም ማጽዳት በሚል አጭር መልእክት አስተላልፌ ነበር አሁንም ያንኑ በተመለከተ ተጨማሪ ማብራሪያና እና መረጃ ለመስጠት ይችን አጠር ያለች ጽሁፍ ማቅረብ ፈለግሁ።
ከዚህ በፊት እንደጠቀስኩት የወያኔ ሰላዮችም ሆኑ እበላ ባዮች የኢትዮጵያ መንግስት አሰረኝ፤ ገረፈኝ፤ አሰቃየኝ ብለው የስደተኝነት ጥያቄያቸው ተቀባይነት በገኘ ማግስት ከወያኔEthiopian spy in London, UK ባለስልጣናትና ኢምባሲ ሰራተኞች ጋር ሲሞዳሞድ እና ሌሎች በትክክል ወያኔ አላኖር ብሏቸው የተሰደዱትን ሲተናኮሉ ይገኛሉ። ከዛም አልፈው እገልሀላሁ በሚል ዛቻ እያሰፈራሩ መሆኑን አይተናል፡ የስደተኛ ተቀባይ ሐገራት ህጎች በትክክል እንዳሰፈሩት ማንም ሰው ዋሽቶ ጥገኝነትን መጠየቁ ከተረጋገጠ ወዲያው ከሀገር እንዲወጣ ይደረጋል ይላል።
አንድ ግለሰብ የወያኔ መንግስት በፖለቲካ አመለካከቴ፤ በዘሬ፤ በሃይማኖቴ እና የመሳሰሉትን ምክንያቶች አቅርቦ አላኖር አለኝ ብሎ የፖለቲካ ጥገኝነት ከጠየቀ ያ መንግስት እስካልተቀየረ ድረስ ችግሩ እንዳለ ነው ተብሎ ስለሚታመን ወያኔ በሚያዘጋጀው ስብሰባ ላይ መገኘት፡ በወያኔ ካድሬወችም ሆነ ደጋፊዎች በሚዘጋጁ የድጋፍ ሰልፎች ላይ መገኘት፡ የወያኔ ባለስልጣናት ባዘጋጁት ድግስና ስብሰባ ላይ መገኘት፡ በሁለት መልኩ ሊታይ ይችላል፡
  1. ያ ግለሰብ ምንም ብሎ ይመጣ የወያኔ ሰላይ ነው ወይም
  2.  ጥገኝነት ሲጠይቅ ያቀረባቸው ምክንያቶች ውሸት ናቸው፡
ከሁለት አንዱ ሆነው ከተገኙ ደግሞ የሀገራቱን ህግ ተላልፈዋል፡ አገራቸውም ቢገቡ ምንም ችግር እንደማይገጥማቸውና ፊትም ችግር እንዳልነበረባቸው ስለሚያመለክት ተመልሰው አገራቸው መግባት አለባቸው።

Sunday, February 17, 2013

አባት ያቆየውን በማፍረሱ የሚመፃደቅ ሰራዊት!



የሰሞኑ የአዲስ አበባ ከራሞት እና የቴሌቭዥን ጣቢያዋ የዜና ርዕስ ”የመከላከያ ሰራዊት ሳምንት” ተከበረ የሚል ነበር። በ አዲስ አበባም የኢትዮጵያ ሰራዊት” የደረሰበት የእድገት ድረጃ”
Ancient Ethiopian army
ጥንታዊው የኢትዮጵያ ወታደር
ተብሎ በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች የተሰሩ፣ የተገጠሙ፣ እየተባሉ የተነገሩ አውደ ርዕዮች ከመታየታቸውም በላይ በትናንትናው እለት በአዲስ አበባ ስታድዮም ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማርያም በተገኙበት ኢህአዲግ ለመጀመርያ ጊዜ ወታደራዊ ትርኢት አሳይቷል። መቸም ማንም ዜጋ የሀገሩ ሰራዊት ጠንካራ መሆኑን እና ሃገርን የመጠበቅ አቅም እንዲኖረው ይመኛል። ይህ ሁሉንም የሚያስማማ ጉዳይ ነው።
አሁን ባለንበት አለም ውስጥ የወታደራዊ ጥበብ የጉልበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ ውስብስብ እውቀትን እና ግንዛቤን የሚጠይቅ ሳይንስ ነው። ወደሚፈለገው የእውቀት ደረጃ ለመድረስ ግን አንድ ሰራዊት ማሟላት የሚገባው ብዙ ነገሮች አሉ። በኢህአዲግ የተደራጀው የኢትዮጵያ ሰራዊትን ሳስበው ብዙ ያልተመለሱልኝ  ጥያቄዎች አሉ። ከእነኝህ ጥያቄዎች ውስጥ -
  • ሰራዊቱ የቆመው ለስልጣን መጠበቅያነት ነው ወይንስ ለሕግ እና ለስርዓት ብቻ?
  • ሀገር የመከላከል ሥራ እግረመንገድ የሚስራ ሥራ ነው ወይንስ ቅድምያ የሚሰጠው?
  • ሉአላዊነት (soverginity) የሚለውን ቁልፍ ቃል ሰራዊቱ ከከፍተኛ መኮንኖች እስከ የመስመር መኮንኖች ብሎም እስከ ተራው ወታደር ድረስ በምን ያህል የዲግሪ ደረጃ ይረዳዋል?
  • ሰራዊቱ ኢትዮጵያን እንዴት ነው  የሚገልፃት?
  • ሰራዊቱ በምን ያህል ደረጃ ከአካባቢያዊ የወንዝ ስሜት እርቆ በብሔራዊ ስሜት ውስጥ ነው? መኮንኖቹ ምን ይህል አለምአቀፋዊ ስልታዊ (strategic) የኃይል አስላለፎችን ይረዳሉ? የመተንተን አቅማቸውስ? ወዘተ ከብዙ በጥቂቱ የምነሱብኝ ጥያቄዎች ናቸው።

ኢትዮጵያውያንን አንድ ያደረገ ምሽት




Artist and activist Tamagne Beyene in Norway, Oslo
የዳመነው ችግር፣ ሰማዩ እስኪጠራ፤ ካገር ተሰደድን በተራ በተራ። አንድ ቀን ይታየኛል፡ ታብሶ የኛ ዕንባ፤ እጅ ለእጅ ተያይዘን አገር ቤት ስንገባ። ይህ ዜማ በአንድ ወቅት ቴዲ አፍሮ በአሜሪካ አገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባቀረበው የሙዚቃ ዝግጅት ላይ በአገር ፍቅርና ናፍቆት ለሚሰቃየው አገር ወዳድ እጅ ለእጅ አያይዞ ያላቀሰበት ዘፈን ነበር። እኛም ዛሬ በፎቶው እንደሚታየው ለኢትዮጵያ ህዝብ አይንና ጆሮ በመሆን የሚያገለግለውን የእሳትን መለያ ካኔተራ በመልበስ በእሳት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ምሽት ላይ በኖርዌ የምንገኝ ስደተኞች ከአጭር ድራማ በኋላ የዘመርነው መዝሙር ነው።

Friday, February 15, 2013

ኢትዮጵያ፡ ከዚህ በኋላ ቀጣዩ ጉዟችን (ወይም መቆሚያችን) ወዴት ነው?



በዴሞክራሲ የአንድነት ጎዳና ላይ?
በጁን 2012 ‹‹ኢትዮጵያ፡ በሕገመንግስታዊ ዴሞክራሲ ጎዳና ላይ›› የሚል ጦማር አቅርቤ ነበር፡፡ ‹‹በርካታማ ሕበረሰቦች ከጭቆና ወደ ዴሞክራሲ ሽግግርን ሲያስቡና ሲንቀሳቀሱ፤ እንቅስቃሴያቸውን የሚገቱ በርካታ ፈተናዎች›› እንደገጠሟቸው በማስረጃ የተደገፉ ታሪካዊ እውነታዎችን ጠቅሼ ነበር:-
ከአረብ ‹‹መነሳሳት››ከታየው ልምድ በመነሳት ሕገ መንግስታዊ ቅድመ ውይይት እንደሚያስፈልግ ጠቁሜ አንዳንድ ሃሳቦችም ሰንዝሬ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ሕገ መንግስት ፍለጋና የዴሞክራሲያዊ ሕገ መንግስት ግቡ ዙርያ ጥምጥም መንገድ፤ አድካሚና ተስፋ ሞጋች ይሆናል፡፡ይም ሆኖ የማይቻል አይደለም………..ግጭትን አስወግዶ ሰላማዊ ሽግግርን ተግባራዊ ለማድረግ፤ተፎካካሪ አለያም በተናጠል ያሉት ሁሉ በአንድ ላይ መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ ይሄ ደግሞ በዋናው ግብ ላይስምምነትንና መቻቻልን መግባባትን ይጠይቃል፡፡ በዚህ የሽግግር ወቅት ሕዝባዊ የሲቪክ ማሕበረሰብን በአዲሱ ሕገ መንግስት ዙርያ ማስተማርን ያካትታል፡፡ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ድርጅቶች፤ አመራሮች፤ ምሁራን፤ ሰብአዊመብት ተሟጋቾች፤ እና ሌሎችም የጉዳዩ አካላት፤ ስርአት ባለው ፕሮግራም ተካተው ትምህርትና አስተባብሮ ማሰለፍን መውሰድና ማዳረስ በዚህም ለዴሞክራሲ ሽግግር የሚጠቅመውን ሁሉ ተግባራዊ ማድረግ  ይኖርባቸዋል፡፡ ከጭቆና ስርአት ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርአት ስኬታማ የሆነ ሂደት ለማድረግ ኢትዮጵያዊያን የመነጋገርንና የመመደራደርን ጥበብ ሊማሩ ይገባል…….››

Dr. Tekeda Alemu and TPLF



I am obliged to write this short note after I heard the new Ethiopian UN Ambassador Tekeda Alemu’s, my former bigEthiopian UN Ambassador Tekeda Alemu boss, interview on the EPRDF pal-talk gezategaru a week earlier. The points he forwarded in the interview are provocative and therefore demand a reply and correction. He cannot escape using the usual EPRDF deceiving tactic of making up a story to disguise itself as being somebody that it really is not. From my personal knowledge of the person
The ambassador mentioned that the reason he returned in 1974 to Ethiopia after he completed school in the USA was because he believed the Derg was progressive at the time and Ethiopia was at war with Somalia.

“የሰከነው ትግል” በጋንዲ ምድር ተዘራ፣ ስለ መሬት ነጠቃው ኢህአዴግ




Solidarity Movement for New Ethiopia on Ethiopia's land grab
“መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው” የንግግሩ መግቢያ ነበር። “በጨለማ ውስጥ ነን። ከፍተኛ በደል እየተፈጸመብን ነው። ለመረጃ ሩቅ የሆኑ ሰዎች፣ የስልጣኔ ጮራ ያልበራላቸው ሰዎች፣ የመማር ዕድል ያላቸኙ ሰዎች፣ ግፍ እየተፈጸማባቸው ነው። መብታቸውና ሰብዓዊ ክብራቸው ተረግጧል። በጉልበት መሬታቸው እየተነጠቀ በልማት ስም እየተሸጠ ነው። ይህ ሁሉ የሚደረገው በህንድ ህዝብና መንግሥት ስም ነው። ይህ አሳዛኝ ተግባር በስማችሁ እየተከናወነ ነው። በናንተ ስም። ተቃወሙ። ታገሉ። አግዙን። ለዚህ ነው መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው የምለው” ይህ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ንግግርና የትግል ጥሪ የቀረበው ህንድ ታዋቂው በሆነው ጃዋሃርላል ኔህሩ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፊትለፊት ነበር።

ቀባሪ ያጣው የወያኔ/ኢህአዴግ የአገዛዝ ስረአትና ባለቤት የሌላት ኢትዮጵያ





እንደ ወያኔ/ኢህአዴግዊ ሀገርንና ትውልድን የሚያጠፋ እኩይ አመለካከትና ምግባር ይዞ ተነስቶና ተሳክቶለትም የሚገዛ ከኢትዮጵያ ውጭ በአለም ላይ ያለ ሀገርም ሆነ የሚገዛ ህዝብ የለም። እንደ ወያኔ/ኢህአዴግ የገዛ ወገኑንና ሀገሩን በጠላትነት ፈርጆ፣ ታጥቆና ተደራጅቶ የሚወጋና የሚያፈራርስ የለም። እንደ ወያኔ/ኢህአዴግዊ አገዛዝም ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊንን የማጥፋቱንና የመበታተኑን ምግባር እንዲያቆም እሽሩሩ የተባለና እየተለመነ ያለ የለም።…..
በልመና ቢሆን…..
ፍትህ – እኩልነት
በልመና ቢሆን…
ነጻነት – አንድነት
በልመና ቢሆን….
ሰላምና ሕይወት፤

Freedom


Monday, February 11, 2013

አቶ ስብሓት ነጋ ፍርዳቸውን ሲጨርሱ…



ሐራ ዘተዋሕዶ
  • ‹‹ዕርቅ ለመፈጸም በማለት ሰዎችን ሲልኩ የነበሩ ቄሶች መሰቀል አለባቸው፡፡››
  • ‹‹ታምራት ቤተ ክርስቲያኒቱን ይቅርታ ሊጠይቅ አይችልም፡፡››
  • ‹‹[ሲኖዶስ ማቋቋም] በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከግራኝ ከጉዲት የባሰ ትልቅ  ወንጀል ነው፡፡››
  • <‹ኣቦይ ስብሃት አረጋዊ ናቸው፤ ይሄ የመነጣጠል አባዜ ቢቀርባቸውና ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደው የተጣላ ቢያስታርቁይሻላቸዋል፡፡. . .አርባ ዓመት ሙሉ ቀውስ አታቀጣጥሉ በሉልኝ፡፡›› /አቶ ኣስገደ ገብረ ስላስ ለኢትዮ ምኅዳርጋዜጣ/
ላይፍ፡- አንድ ጉዳይ እናንሣ፡፡ በአሜሪካን አገር የሚገኘው የኦርቶዶክስ ሲኖዶስም ኾነ አራተኛው ፓትርያሪክ ወደ አገር መምጣት የለባቸውም በማለት ደጋግመው ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ ይህ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባት አይኾንም?
Tigray People Liberation Front Split
(አቶ ስብሓት ዛሬ ለንባብ ከበቃው ላይፍ መጽሔት ጋራ ካደረጉት ቃለ ምልልስ)
አቶ ስብሓት፡- የተናገርኹት እንደ አማኝ እና እንደ ዜጋ የግል አመለካከቴን ነው፡፡ መጀመሪያ ፓትርያሪኩን ከኢትዮጵያ የሚያወጣቸው ምክንያት አልነበረም፡፡ ፓትርያሪኩ ኢሕአዴግ ይነካኛል የሚል እምነት አልነበራቸውም፤ ምክንያቱም እንደማንነካቸው ያውቃሉ፡፡ ብንነካቸው እንኳን መሰየፍ ነበረባቸው ወይም ገዳም ገብተው መመነን ነበረባቸው ወይም ኢየሩሳሌም መሄድ ነበረባቸው፡፡
ይህንን ሁሉ ትተው በመጨረሻ ግን ወደ አሜሪካ ወሰዷቸው፡፡ ይህም ሳያንስ በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ ትልቅ ወንጀል በመፈጸም ሲኖዶስ አቋቋሙ፤ የእስልምና አክራሪ እንቅስቃሴን ደገፉ፡፡ እነዚህን ነገሮች ስሰማ ሐሳቤን ገለጽኹ፡፡

አርቲስትና አክትቪስት ታማኝ በየነ በኦስሎ፣ ኖርዌይ (ልዩ አጭር ጥንቅር


የዛሬዋ የእሁድ ምሽት ከታማኝ የኦስሎ የኢሳት ገቢ ማሰባሰብያ መርሃ ግብር ጋር ያሳለፍኩት ምሽት ነበር። ምንም እንኳን መርሃግብሩን በሙሉ ለመፈፀም ባልችልም የአክትቪስት እና አርቲስት ታማኝን በቪድዮ የተደገፈ ገለፃ ግን ለመከታተል እድሉ ገጥሞኛል።
Ethiopian satellite television, norway
ኦስሎ ለኢሳት ገቢ ማሰባሰብያ መርሃግብር ከተገኘው ሕዝብ በከፊል (photo GUDAYACHN BLOG EXCLUSIVE)
ገብስማ ፀጉሩ ከነጭ ሸሚዝ እና ሽሮ መልክ የያዘ ክራቫት ጋር ታማኝን ግርማ ሞገስ አጎናፅፎታል። ታማኝ ወደ መድረኩ ሲመጣ ከታላቅ አክብሮት ጋር ከአምስትመቶ በላይ የሆነው ታዳሚ ከመቀመጫው ተነስቶ ተቀበለው። ታማኝ አፀፋውን እየመለሰ ምስጋናውን ገለፀ። ቀደም ብለው ከጎናቸው ከነበረው ሰው ጋር ይነጋገሩ የነበሩ ሰዎች በፀጥታ ወደመድረኩ ማስተዋል ጀመሩ። ታማኝ ሰላምታውን በአማርኛ ብቻ አልነበረም ያቀረበው ”አሰላም አለኩም” በማለት ለሙስሊም ኢትዮጵያውያን ያለውን አክብሮት ሲገልፅ ሞቅ ያለ ጭብጨባ ተቸረው። ላፕቶፑን አስተካክሎ ከጀርባው በኩል ወዳለው ስክሪን ተመለከተ ትክክል ነው። ንግግሩን ቀጠለ እና እንዲህ አለ-
”ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው በስቶኮልም እና በጄኔቭ ከተመለከትቁት ሕዝብ ኦስሎ ዛሬ የበላይነቱን ይዟል።” ጭብጨባ አጀበው ቀጠለና:-
”…እኔ አርቲስት ነኝ በአርቲስትነት መኖር እችል ነበር። መፅሐፉ የሚለው ከፊትህ ውሃና እሳት ቀርቦልሃል እጅህን ወደወደድከው ጨምር ነው። እኔ እጄን ወደ ውሃ ከትቼ በአርቲስትነቴ እየደነስኩ መኖር አያቅተኝም ነበር። ነገር ግን የእውነት ጉዳይስ? የኢትዮጵያ ጉዳይስ? ዝም ብሎ የሚኖር ህሊና አለን?… እድሜዬ እንደምታዩኝ ላይሆን ይችላል። ፖለቲካ ያቃጥላል፣ ያናድዳል። ሆኖም ግን እስከመጨረሻ ለመፅናት ነው ቃል የገባሁት።”

Friday, February 8, 2013

ፍቅርና አንድነት ያለው ህዝብ ጠላቱን ያሸንፋል



ባለፈው ሂትለርና የወያኔን መሪዎች ባነጻጸርኩበት ጽሁፍ ላይ መለስ ስብሀት በአማራው ህዝብ ላይ በሰፊው ሊያንቀሳቅሱ የሞከሩት እልቂት አንዴት በሚፈልጉት ልክ እንዳልገፋላቸው ሗላ ላይ እናወጋለን ብየ ነበር።
በአለማችን ያሉ ጤናማ መንግስታት በዜጎቻቸው መካከል የመብት ልዩነትና የዘር የቀለም መለያየት፤ ግጭት እንዳይኖር ያለመታከት ይሰራሉ። ይተጋሉ። በኢትዮጵያ ያለው የዲያቢሎሶች መንግስት፤ ሰው በዘሩ ተለይቶ እንዲታወቅ፤ እንዳይስማማም እንዲበላላም ለማድረግ በትጋት ሲሰራ ሀያ ሁለት አመታትን አስቆጠረ።

Charges renewed against Ethiopian journalist Temesghen Desalegn



charges against Ethiopian journalist Temesghen Desalegn
Nairobi, February 8, 2013–The Committee to Protect Journalists condemns the revival of criminal charges against Ethiopian journalist Temesghen Desalegn today in what appears to be a politicized court hearing designed to censor one of the few critical voices left in the country.
A judge in the Federal High Court in the capital, Addis Ababa, revived three charges against Temesghen, former chief editor of the now-defunct Feteh, and one against the general manager of Mastewal Publishing, the publishing company that formerly printed Feteh, according to local journalists who attended the hearing. Temesghen faces charges of “outrages against the constitution,” defaming the government, and false publication of articles, while the manager of Mastewal Publishing faces an unspecified charge for allowing the weekly to be published. Under Ethiopian law, a printing company is also held accountable for a press offense by a publication that it publishes.

Wednesday, February 6, 2013

ተመስገን ስለ አዲስ ታይምስ እንዲህ አለ፤ “የመለስ ራዕይ በ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄት ተተገበረ!!!”


የሁላችንም መተንፈሻ የነበረችው አዲስ ታይምስ የመንግስት ውቃቢ አልወደዳትም እናም ህትመቷ ተቋርጧል። ይህንን አስመልክቶ ተመስገን ደሳለኝ ይህንን ነግሮናል። መርዷችንን እናንብበውማ፤ ቀጥል ተሜ…
ምንም ጥርጥር የለውም መለስ ዜናዊ ፍፁም አምባገነን 

ነበር፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ከአንድ ክፍለ ጦር በላይ የተለየ ሀሳብን እና ነፃ ሚዲያን ይፈራል፡፡ ምንም ጥርጥር የለውም ወራሾቹም ሀሳቡን በነፃነት የሚገልፅን ከመለስ በባሰ መልኩ ይፈራሉ፡፡ ይህ ፍራቻቸው ወደ ጭፍን አምባገነንነት ስለቀየራቸው መላ ሀገሪቷን ወደ ድቅድቅ ጨለማ እየገፏት ነው፡፡
የሆነ ሆኖ መለስ ከአደባባይ ከራቀ በኋላ በፍትህ ቤተሰቦች የሚመራ ትልቅ ሚዲያ ሲዘጋ ‹‹አዲስ ታይምስ›› ሁለተኛዋ ናት፡፡
ለ‹‹አዲስ ታይምስ›› መዘጋት መንግስት የሰጠው ሶስት ምክንያት፡-

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ሳስበው!



«ልጆቼን ከተወለዱ ጀምሮ ለ20 ቀናት ያህል ስለያቸው ይህ የመጀመሪያዬ ነው። ለዚህ ብርታት እና ፅናት እንዲሆነኝ ግን ዘወትር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን አስበዋለሁ። የእስክንድር
Eskinder Nega and his Son Nafkot
እስክንድር ነጋ እና ልጁ ናፍቆት
ልጅ የተወለደው አሁን እርሱ የሚገኝበት እስር ቤት ውስጥ ነው። የሕወሃት ደጋፊዎች ይህንን ሕዝብ ከደርግ ገላገለው እያሉ የሚያደንቁት ስርዓት እርጉዝ ሴት እስር ቤት ውስጥ እንድትወልድ ያደረገ ግፈኛ እንደሆነ ሁሉም ያውቃል። ይህም ሳይበቃቸው ልጁ አምስት ዓመት ሞልቶት እስክንድር ከትምህርት ቤት ሲመልሰው ነበር ድንገት ይዘውት የሚወደው አንድ ልጁ ፊት እጁን ወደኋላ የፊጥኝ አስረው በቪድዮ እየቀረጹ የወሰዱት፣ አሁን የርሱን ልጅና የኔን ልጆች ሳወዳድር የኔ ልጆች በምንም መለኪያ ከ20 ቀናት በኋላ እንደሚያዩኝ እርግጠኞች ናቸው። የእስክንድር ልጅ ግን አይችልም።»
(አርቲስት ታማኝ በየነ አድላይድ/ደቡብ አውስትራሊያ እ.ኤ.አ ጁላይ 2012 )
እውቁ ኢትዮጵያዊ የነፃ ፕሬስ ጀግና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ “አሸባሪ” ተብሎ ለዘጠነኛ ጊዜ የወያኔ እስር ቤት ውስጥ ከተዘጋበት እነሆ ድፍን 16 ወራት ተቆጥረዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥ ብርቅዬው የኢትዮጵያ ልጅ በፈጠራ ወንጀል ያለአግባብ መታሰሩን በመቃወም በአገር ውስጥ የወያኔን የአፈና ድር በጣጥሶ የተደረገ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ባይኖርም፣ በውጭ አገር የሚገኙ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን ግን አልፎ አልፎም ቢሆን ድምፃቸውን በልዩ ልዩ መልክ በማስተጋባት ላይ ይገኛሉ።

Tuesday, February 5, 2013

ትግሉ የሚጠይቀውን መሰዋእትነት ለመክፈል እኛም ዝግጁዎች ነን!

Ginbot 7 weekly editorialቅኝ ገዥዎችን በማሳፈር በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ተጋድሎ ነጻነቷን ጠብቃ የኖረችውና በባርነት ስር ለቆዩ ሀገራት ፋና ወጊ የሆነችው ውድ ሀገራችን ኢትዮጵያ፤ ዛሬ በሀገር ውስጥ ወራሪ በሆነው ህወሃት/ወያኔ መዳፍ እጅ ገብታ በሁሉም ረገድ ከኢኮኖሚ እስከ ሰበአዊ መብት አያያዝ በአለም የመጨረሻዋ የሰው ልጅ መብት ረገጣ የሚፈጸምባት ተስፋ አልባ ሀገር ተብላ ተመድባ ትገኛለች።
ይህችው የቀድሞዋ ኢትዮጵያ በክብርና በኩራት የአፍሪካ የነጻነት ፋናወጊ ተብላ የሚነገርላት፤ በዚህ ዘመን በባርነት አረንቋ እየኖረች፣ ህዝቧ የነጻነት ያለህና የትውልድ የድረሱልኝ ጥሪ ኤሎሄ ለወጣት ልጆቿ  እያቀረበች፣ እየተማጸነች አለች።
ይህን ተከትሎ በሁሉም ግንባር ሀገር በቀል ወራሪ ህወሃት/ወያኔን ታግሎ ለማስወገድ እየተደረገ ያለው ትብብር የሚበረታታ ቢሆንም የወያኔን የከፋፍለህ ግዛ ና የአንድ ዘር የበላይነት ርዕዮተ ዓለምን አስወግዶ ነፃነት ከናፈቀው ህዝብ ጎን በመሰለፍ በሀገራችን የሰላም አየር በሁሉም ከተሞች እንዲሰፍን ለሚደረገው እልህ አስጨራሽ ጉዞ የምናደርገው እገዛ በቂ ነው ብለን አናምንም።